አሳዛ ኝ ዜና‼️

በምስራቅ ወለጋ ዞን ጊዳ አያና በህዝብ ማመላለሻ አውቶብስ ላይ በደረሰ #የትራፊክ_አደጋ የ16 ሰዎች ህይወት ማለፉ ተገለፀ።

በኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን የትራፊክ ቁጥጥር ደህንነት የሥራ ሂደት ከፍተኛ ባለሙያ ኮማንደር ንጉሴ ግርማ ለfbc እንደተናገሩት፥ አደጋው በትናነትናው እለት ነው የህዝብ ማመላለሻ ኤፍ.ኤስ.አር ተሽከርካሪ ተገልብጦ የደረሰው።

የህዝብ ማመላለሻ አውቶብሱ ላይ በደረሰው የመገልበጥ አደጋም የ16 ሰዎች ህይወት ወዲያውኑ ሲያልፍ 10 ሰዎች ላይ ከፍተኛ ጉዳት እንዲሁም 5 ሰዎች ላይ ደግሞ ቀላል ጉዳት መድረሱንም ኮማንደር ንጉሴ አስታውቀዋል።

ምንጭ:- fbc
@tsegabwolde @tikvahethiopia