Audio
"ታጣቂዎች "መከላከያ ሰራዊት" ላይ ተኩስ ከፍተዋል" የመከላከያ ሰራዊት
.
.
በአማራ ክልል ምዕራብ ጎንደር ገንደ ውሃና ኮኪት በተባለ ቀበሌ ከመከላከያ ሰራዊት አባላት በተተኮሰ ጥይት 27 ሰዎች መመታታቸውንና ከእነዚህ ውስጥ ሰባት ሰዎች ደግሞ መሞታቸውን የዓይን እማኝ መሆናቸውን የተናገሩ ነዋሪዎች ለአሜሪካ ድምጽ ገለፁ። ግድያውንም በመቃወም ዛሬ የተቃውሞ ሰልፍ ማድረጋቸውን ተናግረዋል። የሆስፒታል ምንጮች ሰዎች መገደላቸውንና መቁሰላቸውን ነግረውናል። የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ጦር ኃይሎች ምክትል ኢታማዦር ሹም ጀነራል #ብርሃኑ_ጁላ በበኩላቸው በአካባቢው በመንገድ ሥራ ላይ የተሰማራ ኩባንያን አጅቦ በመውጣት ላይ በነበረ የመከላከያ ሠራዊት አባላት የታጠቁ ሰዎች ተኩስ መክፈታቸውን ገልፀዋል።

ምንጭ፦ VOA
@tsegabwolde @tikvahethiopia