#Update የጉጂ ኦሮሞ አባገዳዎች አለመግባባቶች #በድርድር እንዲፈቱ ፣ የህግ የበላይነት እንዲከበርና ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን ጥሪ አቀረቡ፡፡ በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር ውይይት ከተደረገ በኋላ ጥር 2 ቀን 2011 ዓ.ም. በነገሌ ከተማ በባህላዊ የገዳ ስርዓት የሰላም ሳምንት እንደሚታወጅ አባ ገዳ ጂሎ ማኖ አስታውቀዋል። የሰላም ሳምንትን አስመልክቶ ከአዶላና ሻኪሶ ወረዳዎች የሀገር ሽማግሌዎችና ከኃይማኖት አባቶች እንዲሁም ከሌሎች ነዋሪዎች ጋር የሰላም ውይይት መደረጉን ገልጸዋል፡፡ አባ ገዳ ጂሎ ማኖ የሰላም እጦት ጎልቶ በሚታይበት በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ጉጂ ዞን ካለፈው ሰኞ ጀምሮ የሰላም ሳምንት መታወጁን አስታውሰዋል፡፡

ምንጭ፦ ኢዜአ
@tsegabwolde @tikvahethiopia