አሳዛኝ ዜና‼️

በወረታ ከተማ የአደጋ መከላከያ እህል ክምችት መካዝን አካባባቢ በደረሰ #የትራፊክ_አደጋ የሰው ህይወት አለፈ።

በትላንትናው ዕለት ከጎንደር ወደ ባ/ዳር ሲጓዝ የነበረ የሰሌዳ ቁጥር ET 78608 የሆነ ዳንጎቴ የከባድ ጭነት መኪና መንገዱን በመሳት ከወረታ ወደ ወርቅ ሜዳ ሲጓዝ ከነበረ የሰሌዳ ቁጥሩ 23141 ከሆነ ባጃጅ ጋር #በመጋጨቱ ከባጃጁ ውስጥ ሆነው ሲጓዙ ከነበሩት 5 ተሳፋሪዎች መካከል 2ቱ ወዲያውኑ ህይወታቸው አልፏል።

በአደጋው 1 ሰው ከባድ ጉዳት የደረሰበት መሆኑንና ወዲያዉኑ ወደ ፈለገ ህይወት ሆስፒታል በአንቡላንስ መላኩንና 2ቱ ደግሞ ቀላል ጉዳት ደርሶባቸው በወረታ ከተማ ጤና ጣቢያ እየተረዱ መሆናቸውን የወረታ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጽ/ቤት ከስፍራው መዘገቡን የጽ/ቤቱ የህዝብና ሚዲያ ግንኙነት የለውጥ ቡድን መሪ አቶ ኃይሌ ብርሃኔ አስታውቀዋል።

ምንጭ፦Woreta city communication affairs(Mulusew)
@tsegabwolde @tikvahethiopia