ባይደዋ‼️

በሶማሊያዋ ባይደዋ ከተማ ለሁለተኛ ቀን #ብጥብጥ እንደቀጠለ እማኞች ገለፁ። የብጥብጡ መንስኤ በትናንትናው ዕለት የቀድሞ የአሸባብ መሪ እና የአሁኑ ፕሬዝደንታዊ እጩ ሙክታር ሮቦው በወታደሮች በቁጥጥር ሥር መዋሉ ነው። ዛሬ የሮቦው ደጋፊዎች ከፀጥታ ኃይላት ጋር ተጋጭተዋል፤ 11 ሰዎችም ተገድለዋል። DW ያነጋገረው አንድ ሶማሊያዊ ጋዜጠኛ ሮቦውን የተያዘው በኢትዮጵያውያን ወታደሮች መሆኑን ገልጿል። እንደ ጋዜጠኛው ቀደም ሲል የሶማሊያ መንግሥት በተለይም የፀጥታ ኃይሉ ሮቦው ለምርጫ መቅረቡን ተቃውሞ ነበር።

ምንጭ፦ DW የአማርኛው አገልግሎት
@tsegabwolde @tikvahethiopia