ትምህርት ሚኒስቴር‼️

ትምህርት ሚኒስቴር ነገ #በፍኖተ_ካርታው ዝግጅት ዙሪያ ጋዜጣዊ #መግለጫ ይሰጣል፡፡

የትምህርት ሚኒስትር ለቀጣዮቹ 15 ዓመታት ተግባራዊ የሚሆን አጠቃላይ የትምህርት ፍኖተ ካርታ እያዘጋጀ እንደሆነ ከዚህ ቀደም ተገልጧል፡፡

የፍኖተ ካርታው ዝግጅት ለሚመለከታቸው አካላት በየደረጃው ለውይይት ቀርቦ ግብዓት እንደተሰጠበት ትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡

የፍኖተ ካርታው ዝግጅት የደረሰበትን ደረጃ በሚመለከት ነገ በትምህርት ሚኒስትር የስብሰባ አዳራሽ ከጠዋቱ 3፡00 ስዓት ጀምሮ የትምህርት ሚኒስትሩ ዶክተር #ጥላዬ_ጌቴ መግለጫ ይሰጣሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡

ምንጭ፡- ትምህርት ሚኒስቴር
@tsegabwolde @tikvahethiopia