ሰበር ዜና‼️

በኦሮሚያና ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልሎች አዋሳኝ ካለው የፀጥታ ችግር ጋር በተያያዘ እስካሁን 208 #ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ውለዋል።
.
.
.
በኦሮሚያና ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልሎች አዋሳኝ አካባቢ ላይ የህግ የበላይነትን ለማስፈን #በፀረ_ሰላም_ሀይሎች ላይ እየተወደሰ ያለው እርምጃ ተጠናክሮ መቀጠሉ ተገለፀ።

የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ የገጠር ፖለቲካ አደረጃጀት ዘርፍ ሃላፊ አቶ አዲሱ አረጋ በማህበራዊ ሚዲያ ገጻቸው እንዳሰፈሩት፥ በክልሎቹ አዋሳኝ አካባቢ ላይ የፀጥታ ችግር እንዲከሰት አድርገዋል ተብለው በቁጥጥር ስር የዋሉ ተጠርጣሪዎች ቁጥር 208 ደርሷል።

የህግ የበላይነትን ለማስፈን እየተወሰደ ያለው እርምጃ ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑንም ነው አቶ አዲሱ ያስታወቁት።

በአሁኑ ወቅት በአካባቢው ያለው ሰላም እየተሻሻለ መምጣቱንም ገልፀዋል። በቀጣይም በአካባቢው አስተማማኝ ሰላም እንዲረጋገጥ በማድረግ ከቀያቸው የተፈናቀሉ ሰዎች እንዲመለሱ ለማድረግ ከፍተኛ ትኩረት ተሰጥቶት የሚሰራ መሆኑንም ነው አቶ አዲሱ ያስታወቁት።

ምንጭ፦ fbc
@tsegabwolde @tikvahethiopia