ደብረ ታቦር‼️

በደቡብ ጎንደር መስተዳድር ዞን የደብረ ታቦር ማረሚያ ቤት ትላንት ከቀኑ 11፡00 አካባቢ #አለመረጋጋት ተከስቶ ነበር።

ከቀኑ 11፡00 አካባቢ መደበኛው የታራሚዎች ቆጠራ የሚያደርጉ የመምሪያውን የፖሊስ አባላት #በማፈን እስረኞች #ለማምለጥ በመሞከራቸው ነው አለመረጋጋቱ የተፈጠረው።

የፖሊስ አባላቱን በማፈን ግርግር ፈጥረው ለማምለጥ ሙከራ ያደረጉት ደጋጋሚ እስረኞችና ከባድ ፍርደኞች መሆናቸውን የደብረ ታቦር ማረሚያ ቤት መምሪያ ኃላፊ ምክትል ኮማንደር መንጌ ከበደ ተናግረዋል፡፡

የመምሪያ ኃላፊው ለአማራ ብዙኃን መገናኛ ድርጅት እንዳስታወቁት ተጨማሪ የፖሊስ ኃይል በመጨመር የማረሚያ ቤቱን ሰላም የማረጋጋት ሥራ ተሰርቷል።

ምንጭ፦ አ.ብ.መ.ድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia