ኮንጎ‼️

የዓለም ጤና ድርጅት ሰራተኞቹን ከምስራቃዊ ኮንጎ #አሸሸ። የድርጅቱ ሰራተኞች #የኢቮላ_ወረረሽኝ በተስፋፋባት ቤኒ በሽተኞችን እየረዱ በነበሩበት ወቅት በአማፂያንና በሰላም አስከባሪዎች መካከል በተፈጠረ ግጭት ሳቢያ ነው አካባቢውን ለቀው የወጡት፡፡

አጃንስ ፍራንስ ፕሬስ እንደዘገበው የጤና ባለሞያዎቹ የሚኖሩበት ህንጻ በተኩስ ልውውጡ ወቅት በመሳሪያ ተመቷል፡፡

ሰራተኞቹ ላይ የደረሰ ጉዳት ባይኖርም የዓለም ጤና ድርጅት በቤኒ ግዛት የኢቮላ ወረርሽን ከተከሰተ ወዲህ የስጋቱ መጠን በማየሉ ለመጀመሪያ ጊዜ የጤና ባለሞያቹን ለማሸሽ ተገዷል፡፡

የዲሞክራቲክ ኮንጎ የጤና ሚኒስቴር እንዳስታወቀው በግጭቱ ምክንያት ኢቮላን የመከላከሉ ተግባር በመስተጓጎሉ የበርካቶች ህይዎች አደጋ ላይ ነው፡፡

ባለፈው ሳምንት ስድስት የማላዊ ዜግነት ያላቸው የሰላም አስከባሪ ወታደሮች በአማፂዎቹ መገደላቸው ይታወሳል፡፡

ምንጭ፦ አርትስ ቴሌቪዥን
@tsegabwolde @tikvahethiopia