አሳዛኝ ዜና‼️

በካሊፎርንያ መዝናኛ ቤት ውስጥ በተከፈተ ተኩስ የፖሊስ ባልደረባን ጨምሮ #በትንሹ አስራ ሁለት ሰዎች #መሞታቸው ተሰምቷል፡፡

የካሊፎርንያ ፖሊስ እንዳስታወቀው ትላንት ምሽት ቦርደር ላይን ባር ላይ በተከፈተ ተኩስ ከሞቱት አስራ ሁለት ሰዎች በተጨማሪ አስር ግለሰቦች ጉዳት እንደደረሰባቸው አስታውቋል፡፡

ጥቃቱን እንደፈፅመ የተጠረጠረው ግለሰብ በመዝናኛ ቤት ውስጥ ሞቶ የተገኘ ሲሆን እስካሁን ስለማንነቱ ተጨማሪ መረጃ አለማግኘቱን ፖሊስ ተናግሯል፡፡

ተጠርጣሪው አውቶማቲክ መሳሪያ መጠቀሙን የአይን እማኞችን ጠቅሶ ፓሊስ አስታውቋል፡፡

በመዝናኛ ቤቱ ውስጥ ከሁለት መቶ በላይ ሰዎች እንደነበሩ የፖሊስ ቃል አቀባዩ ኤሪክ ቤሹ ጠቁመዋል፡፡

ተጠርጣሪው በመዝናኛ ቤቱ የተኩስ እሩምታውን ከከፈተ በኋላ በስተመጨረሻ እራሱን ሳያጠፋ እንዳልቀረ ፖሊስ ተናግሯል፡፡

ተኩሱን ተከትሎ በርካቶች መስኮት በመዝለል ለማምለጥ የሞከሩ ሲሆን ሌሎች መጸዳጃ ቤት በመደበቅ ህይወታቸውን አትርፈዋል ነው የተባለው፡፡

ምንጭ፦ ሲኤንኤን
@tsegabwolde @tikvahethiopia