ወላይታ ሶዶ⬆️

ከወላይታ ዩኒቨርሲቲ አንዳንድ ግለሰቦች በተማሪዎች ላይ በፈጠሩት የደህንነት ስጋት ገጥሞአቸው የወጡ የሲዳማ ብሔር ተማሪዎች ጉዳዩ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በተደረገው ውይይት #ችግሩ በመፈታቱ ዛሬ ከሲዳማ ዞን አስተዳደርና ከክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጽ/ቤት በተወከሉ አመራር አካላት በመመራት ወደ ወላይታ ሶዶ ያቀኑ ሲሆን ሲደርሱም የወላይታ ሽማግሌዎች፣ የኃይማኖት አባቶች፣ የአመራር አካላት እና የዩኒቨርሲቲ ማህበረ ሰብ፣ የኪነ ጥበብ ባለሙያዎች እንዲሁም ከተለያዬ ኀብረተሰብ ክፍሎች የተወከሉ በተገኙበት #ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል። ለተማሪዎቹ ለተደረገላቸው ደማቅ አቀባበል የሲዳማ ዞን አስተዳደር ታላቅ ምስጋና አቅርቧል።

ምንጭ:- የሲዳማ ዞን ባህል፣ቱሪዝምና የመንግስት ኮሙኒኬሽን መምሪያ

@tsegawolde @tikvahethiopia