#update 10ኛ ክፍል⬇️

በ2010 ዓ.ም የ10ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የፈተና ውጤት እስከ #አርብ ድረስ ይፋ እንደሚሆን የሀገር ዓቀፍ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች ኤጀንሲ አስታውቋል።

የተማሪዎችን እርማት ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ መረጃውን በአጭር ጽሁፍ እና በድረ-ገጽ በጥራት ለማሰራጨት ከሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ጋር እየተሰራ መሆኑን የአገር አቀፍ የትምህርት ምዘና እና ፈተናዎች ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር አቶ አርአያ ገብረእግዚአብሔር ለኢቢሲ ተናግረዋል፡፡

ኤጀንሲው እስካሁን ውጤት በየትኛውም የውጤት ማሳወቂያ ዘዴ እንዳላወጣና ተማሪዎች በኤጀንሲው ስም በሚወጡ #የተሳሳቱ መረጃዎች እንዳይታለሉም አቶ አርአያ አሳስበዋል፡፡

ውጤቱን ይፋ ለማድረግ የሚያስፈልጉ ቅድመ ሁኔታዎች መጠናቀቃቸውንና እስከ መጪው አርብ ድረስ ውጤቱ እንደተለመደው በኤጀንሲው ድረ-ገፅና በአጭር የፅሁፍ መልእክት ይፋ ይደረጋል፡፡

ተማሪዎች የለፉበት ውጤት እንዳይሳሳት በከፍተኛ ጥንቃቄ እየተሰራ መሆኑን የገለፁት ዳይሪክተሩ የ2010 ዓ.ም የ10ኛ ክፍል የፈተና ውጤትን ተማሪዎች #በትእግስት እንዲጠባበቁም ጠይቀዋል፡፡

©etv
@tsegabwolde @tikvahethiopia