#update BiT-ባህር ዳር⬇️

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ቴክኖሎጅ ኢንስቲትዩት የ3ኛ ዓመት ኢንጅነሪንግ ተማሪዎች አጠቃላይ ፈተና (Holistic Exam ) አንፈተንም በማለታቸው የባሕር ዳር ቴከኖሎጅ ኢንስቲትዩት የአካዳሚክ ካውንስል የ3ኛ አመት ተማሪዎች ለአንድ አመት ማለትም 2011 የትምህርት ዘመንን ከትምህርት ገበታ እንዲታገዱ መወሰኑ ይታወሳል፡፡ ይህ ግን የዩንቨርሲቲው ሴኔት ውሳኔ
አለመሆኑን #ተረጋግጧል።

አሁን ላይ ደግሞ ዩኒቨርሲቲው በባሕር ዳርና አካባቢው ያሉ የተማሪዎች ወላጆችን አስቸኳይ ስብሰባ ጠርቶ ሊያወያይ ነው። ውይይቱ ነገ ሰኞ
ነሐሴ 21/2010 ዓ.ም. በቴክኖሎጄ ኢንስቲትዩት ፖሊ ግቢ ከቀኑ 8፡00 ይጀመራል። አወያዩም የዩኒቨርሰቲው ፕሬዝዳንት ዶክተር ፍሬው ተገኘ ናቸው።

ዶክተር ፍሬው ተገኘ ለአማራ ብዙኃን መገናኛ ድርጅት እንደተናገሩት የውይይቱ ዓላማ በተማሪዎቹ እና በቴክኖሎጅ ኢንስቲትዩቱ መካከል የተፈጠረውን ችግር ትክክለኛ ምክንያት ለወላጆች ለማስረዳት እና መፍትሄ ለመሰጠት ነው።

በምዘና መመሪያው ላይ ግን #ማሻሻያ አልተደረገም ነው ያሉት። በመሆኑም ተማሪዎች ፈተናውን ለመፈተን ፈቃደኛ ከሆኑ ትምህርታቸውን እንዲቀጥሉ የዩኒቨርሲቲው ሴኔት #ይቅርታ ሊያደርግላቸው እንደሚችል ነው ፕሬዝዳንቱ የተናገሩት።

©AMMA
@tsegabwolde @tikvahethiopia