TIKVAH-ETHIOPIA
1.47M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#DStvEthiopia #Gojo

🔥ከባድ ትንቅንቅ የማያጣው የ ማንቸስተር ሲቲ ከ አርሰናል በጎጆ ፓኬጅ

🏆 አስተማሪው ከ ተማሪው ጋር ይገናኛሉ! የቱ ቡድን 3 ነጥብ ይዞ ወደ ቀጣዩ ሳምንት ማለፍ ይችላል?

ይህንን ደማቅ ፍልሚያ በጎጆ ፓኬጅ በቀጥታ ይከታተሉ

🎉ዛሬውኑ ደንበኝነትዎን ወደ ጎጆ በማራዘም ጨዋታዎችን ከትንታኔ ፣ ከተጫዋች ብቃትእስከ ቡድን ወኔ በሱፐርስፖርት ይከታተሉ!

ዲኤስቲቪ ያስገቡ ፣ ደንበኝነትዎን ያራዝሙ!
👇
https://bit.ly/3RFtEvh

#DStvEthiopia #ሁሉምያለውእኛጋርነው
HEY Mobile !

Tab A9 - 19,500 ETB
•Tab A8 - 29,500 ETB
•Tab A9+ 5G - 31,000 ETB
•Tab S6 Lite - 47,000 ETB
•Tab S9 FE - 59,000 ETB
•Tab S9 +5G - 99,000 ETB
•Tab S9 Ultra - 129,000 ETB

Contact us :
0936222222 @heymobile1
0925927457 @eBRO4

@Heyonlinemarket
#ዋሪት !

ዘወትር የደንበኞቻችንን ፍላጎት ማርካት ቀዳሚ የሚያደርገው ዋሪት ዛሬም የበርካቶቻችሁን ጥያቄ መሰረት በማድረግ የአዲስ ዓመትን ቅናሽ እስከ መስከረም 16 ቀን 2017 ዓ.ም. ድረስ ማራዘሙን ስንገልፅ በታላቅ ደስታ ነው። የዋሪትን የውሃ ማጣሪያ ለየት የሚያደርገው ከሽያጭ በኋላ ለሚኖር ብልሽት አስተማማኝ የጥገና እና የመለዋወጫ አገልግሎት መስጠታችን !

ትክክለኛ ምርጫ!
ለተጨማሪ መረጃ: ☎️ 0911210706 / 07
TIKVAH-ETHIOPIA
#Amhara " ከ7 ሚሊዮን በላይ ተማሪዎችን ለመመዝገብ ነው እቅድ የተያዘው ከነሐሴ 20/2016 ዓ/ም ጀምሮ የተመዘገቡት ግን 1.7 ሚሊዮን ናቸው - የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ በመንግስት የጸጥታ ኃይሎችና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል በየጊዜው የተኩስ ልውውጥ የሚስተዋልበት አማራ ክልል በ2017 የትምህርት ዘመን ከ7 ሚሊዮን በላይ ተማሪዎችን ለመመዘገብ እንዳቀደ፣ ከነሐሴ 20 ቀን 2016 ዓ/ም ጀምሮ…
#Amhara

“ የእኛ አብዛኛዎቹ ትምህርት ቤቶቻችን ደረጃ 2 ላይ ያሉ ናቸው፡፡ ደረጃቸው ዝቅተኛ ግን መማር ማስተማሩን ማስኬድ የሚችሉ እንደማለት ነው ” - የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ

በአማራ ክልል በተለይ በጸጥታ ችግር ሳቢያ የግብዓት እጥረት ያለባቸው ትምህርት ቤቶች እንዳሉ፣ ይህም ልጆቻቸውን ወደ ትምህርት ቤት ለመላክ ማነቆ እንደሆነባቸው ወላጆች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገጸዋል፡፡

ለአብነትም እንደ መጽሐፍት፣ ወንበር መሰል ቁሳቁሶች እንደሌሉ፣ የወደሙ ትምህርት ቤቶች አለመጠገን፣ በግጭት የቀጠና ውስጥ የሆኑ አቅመ ደካማ ወላጆች ደግሞ ለልጆቻቸው እንኳ የትምህርት ግብዓት ማሟላት እንዳልቻሉ ነው ያስረዱት፡፡

ቲክቫህ ኢትዮጵያም ለጉዳዩ ምላሽ እንዲሰጥ የክልሉን ትምህርት ቢሮ ጠይቋል፡፡

ቢሮው ምን ምላሽ ሰጠ ?

“ የግብዓት እጥረት አለብን ያሉ ትምህርት ቤቶች ይኖራሉ፡፡ ትክክል ነው፡፡ የግብዓት እጥረታቸው በሁለት መንገድ ነው የሚፈታው፡፡

አንደኛ የአካባቢውን ማህበረሰብ በማሳተፍ ነው፡፡ ሁለተኛ ደግሞ በክልል ደረጃ ደግሞ የሚሟሉ አሉ፡፡ ለምሳሌ መጽሐፍት በክልል ነው የምናሟላው፡፡

ከ14 ሚሊዮን በላይ መጽሐፍት ታትመው ስርጭት ተደርጓል፡፡ አሁንም በቀጣይ የሚሰራጩ አሉ፤ ከ1 ቢሊዮን በላይ በጀት የክልሉ መንግስት መድቦ አሁንም የሚታተሙ መጽፍት አሉ፡፡

እነርሱን አሳትመን እናሰራጫለን፡፡ የመምህራን ቅጥርም እናሟላለን፣ ትክክል ነው፡፡

የእኛ ክልል ትምህርት ቤቶች ሙሉ ግብዓት የተሟላላቸው፣ ስንታንዳርዳቸውን ያሟሉ አይደሉም፡፡

ትምህርት ቤቶች በ4 ደረጃ ይከፈላሉ፡፡ ደረጃ 1፣ 2፣ 3 እና ደረጃ 4 ተብለው፡፡ ደረጃ 4 የሚባል ትምህርት ቤት በክልሉ የለንም፡፡

ደረጃውን ያሟላ በጣም ኢንተርናሽናል እንደማለት ነው፡፡ ደረጃ 3 የሚባለው ደግሞ ለተማሪዎች መማር ማስተማር የተሻለ የሆነ ትምህርት ቤት ማለት ነው፡፡

የእኛ አብዛኛዎቹ ትምህርት ቤቶቻችን ደረጃ 2 ላይ ያሉ ናቸው፡፡ ደረጃቸው ዝቅተኛ ግን መማር ማስተማሩን ማስኬድ የሚችሉ እንደማለት ነው፡፡ ይሄ ማለት ብዙ ግብዓት የሚጎድላቸው ናቸው፡፡

ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች 3ቱም ሳይንስ ቤተ ሙከራ እንዲሟላ፣ ደረጃውን የጠበቀ የኳስ ሜዳ እንዲኖረው፣ አጥር እንዲኖረው፣ ስታንዳርዱን እንዲያሟላ፣ ፋሲሊቲውን በማሟላት ረገድ መስራት የሚጠይቀን ሥራ አለ፡፡

እሱን በእቅድ ለመምራት ጥረት እየተደረገ ነው፡፡ ግን ሙሉ የሕብረተሰቡን ተሳትፎ የሚጠይቅ ሥራ ነው፡፡

የእኛን ትምህርት ቤቶች በስንት ዓመት እንቀይራቸዋለን ደረጃቸውን ለማሻሻል ብለን አንድ በጣም ትልቅ የለውጥ እቅድ አቅደን ወደ ሥራ በገባን ማግስት ነው የጸጥታው ችግር የተፈጠረው፡፡

በዚህ ዓመት ውስጥ ትምህርት ቤቶቹን እንቀይራለን ብለን ነበር ዞሮ ዞሮ ወደ ሥራ መግባት አልተቻለም ”
ብሏል፡፡

የግብዓት እጥረት ላለባቸው ከባለሀብቶችና ባለንብረቶች ድጋፍ የማሰብሰብ ሥራ እየተከናወነ መሆኑንም ቢሮው ገልጿል፡፡

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
" መፍትሄ ሳይዘጋጅና በቂ ጥናት ሳይደረግ የተላለፈው ውሳኔ ፍጹም አግባብነት የሌለው ነው " - የትራንስፖርት ዘርፍ ላይ የተሰማሩ አካላት

የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር አማራጭ መፍትሔ ሳያዘጋጅና በቂ ጥናት ሳያካሂድ " ከ30 ዓመት በላይ አገልግሎት የሰጡ ድንበር ተሻጋሪ ተሽከርካሪዎች፣ አገልግሎት እንዳይሰጡ " ብሎ ውሳኔ አስተላልፏል ፤ ይህ ደግሞ አግባብነት የሌለውና ከትራንስፖርት ዘርፍ የሚገኘውን ኢኮኖሚዊ ጥቅም የሚያሳጣ ነው ሲሉ በዘርፉ የተሰማሩ አካላት ቅሬታቸውን አቀርበዋል።

የኅብረት ትራንስፖርት አክሲዮን ማኅበር መሥራችና ዋና ዳይሬክተር አቶ ባይሳ አየለ ምን አሉ ?

" የትንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር ግልጽ የሆነ መመርያ ሳያወጣ፣ ለዓመታት አገልግሎት የሰጡ ድንበር ተሻጋሪ ተሽከርካሪዎች አገልግሎት እንዳይሰጡ ብሏል። ይህ አግባብነት የለውም፡፡

ሚኒስቴሩ በዋናነት እነዚህ ተሽከርካሪዎች አገልግሎት እንዳይሰጡ ያለበት ምክንያት፣ የአየር ብክለትን ለመከላከል አስቦ ነው። መንግሥት እንዲህ ዓይነት አሠራር ሲዘረጋ የብድር አገልግሎትና ተሽከርካሪዎች ከቀረጥ ነፃ የሚገቡበትን ሁኔታ ማመቻቸት ይኖርበታል።

በኢትዮጵያ 60 በመቶ የሆኑ ድንበር ተሻጋሪ ተሽከርካሪዎች ከ30 ዓመታትና ከዚያ በላይ አገልግሎት የሰጡ ናቸው፡፡ ተሽከርካሪዎቹ ደግሞ በምን ዓይነት ሁኔታ ነው የሚቀጥሉት የሚለውን መንግሥት ከዘርፉ ባለድርሻ አካላት ጋር ጠለቅ ያለ ውይይት ማድረግ አለበት " ብለዋል።


የኢትዮጵያ ትራንስፖርት አሠሪዎች ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት አቶ ብርሃኔ ዘሩ ምን አሉ ?

" ለከባድ ተሽከርካሪዎች የሚሆን የመሠረተ ልማት በአግባቡ ሳይሟላ መንግሥት በፍጥነት ተሽከርካሪዎቹ ወደ #ኤሌክትሪክ ይቀየሩ ማለቱ ትክክለኛ አካሄድ አይደለም።

በአሁኑ ወቅት ዕድሜያቸው ከ30 ዓመታት በላይ ያስቆጠረ ድንበር ተሻጋሪ ተሽከርካሪዎቹ የማጓጓዝ አገልግሎት እንዳይሰጡ ፈቃድ በመከልከላቸው፣ እንዲቆሙ ተገደዋል።

ተሽከርካሪዎቹ በብቃትና በጥንካሬ የሚሰጡት አገልግሎት ከፍተኛ መሆኑን ከግምት ውስጥ በማስገባት፣ አስተማማኝ አቅርቦት እስኪኖር ድረስ ተሽከርካሪዎቹ እንዲሠሩ መደረግ አለበት።

ዓመታዊ የብቃት ማረጋገጫ ፈቃድ ለማደስ ጥያቄ ያቀረቡ አብዛኛዎቹ አክሲዮን ማኅበራት ተጨማሪ ተሽከርካሪዎች መግዛት ባለመቻላቸው ፈቃዳቸው አልታደሰም።

በዚህ ምክንያት አክሲዮን ማኅበራቱ ለጭነት አገልግሎት ሥራ በማንኛውም ጨረታ እንዳይሳተፉ ስለሚከለከል ተጨማሪ ተሽከርካሪዎች ለመግዛት ያለው የአቅም ውስንነት ታሳቢ በማድረግ የጊዜ ገደብ እንዲራዘምላቸው መደረግ ይኖርበታል።

ከ30 ዓመታት በላይ አገልግሎት የሰጡ ድንበር ተሻጋሪ ተሽከርካሪዎችን በተመለከተ፣ የተሻለ አሠራር እንዲፈጠርና የንብረቱ ባለቤቶችም ምቹ ሁኔታ እንዲያገኙ ለገንዘብ ሚኒስቴር፣ ለትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴርና ጉዳዩ ለሚመለከታቸው አካላት በተለያዩ ጊዜያት ጥያቄ ብናቀርብም ምላሽ አልተገኘም " ብለዋል።

(ከሪፖርተር ጋዜጣ)

@tikvahethiopia
ባለ ብዙ ቀለሟ ኢትዮጵያ !

(አሁን ላይ እየተከበሩ ያሉና በቀጣይ ቀናት የሚከበሩ በዓላት)

የሀዲያ የዘመን መለወጫ ' ያሆዴ '
የወላይታ የዘመን መለወጫ  ' ዮዮ ጊፋታ '
የካፊቾ የዘመን መለወጫ ' ማሽቃሮ '
የጋሞ የዘመን መለወጫ ' ዮ ማስቃላ ' 
የጊዲቾ የዘመን መለወጫ  ' ባላ ካዳቤ '
የዘይሴ የዘመን መለወጫ ' ቡዶ ኬሶ '
የቦሮ ሺናሻ የዘመን መለወጫ ' ጋሪ ዎሮ '
የጎፋ የዘመን መለወጫ ' ጋዜ ማስቀላ '
የኦይዳ የዘመን መለወጫ ' ዮኦ ማስቃላ '
የከምባታ ዘመን መለወጫ ' መሳላ '
➡️ የጠምባሮ ዘመንድ መለወጫ ' መሳላ '
የዶንጋ ዘመን መለወጫ ' መሳላ '
የየም ዘመን መለወጫ ' ሄቦ '

ይህ የመስከረም ወር በርካታ ብሔር ብሔረሰቦች የዘመን መለወጫ በዓላቸውን የሚያከብሩበት ነው።

#ኢትዮጵያ

እንኳን አደረሳችሁ ፤ መልካም በዓል !

@tikvahethiopia
🔈#የወጣቶችድምጽ

ኢትዮጵያ ከፍተኛ የወጣቶች ቁጥር ያለባት ሀገር ናት።

ካለው ከፍተኛ የወጣቶች ቁጥር አንጻር ያለው የስራ እድል አነስተኛ ነው። የስራ እድል ቢገኝ እንኳን የሚከፈለው ክፍያ ዝቅተኛ በሆኑ ህይወትን መቀየር እና ያሰቡትን ማሳካት ፈተና ነው።

በዚህ ምክንያት ብዙ ወጣቶች የተሻለ ኑሮና ገቢ ፍለጋ ከሀገር ለመውጣት ይፈልጋሉ።

ወጣቶቹ ያደጉ ሀገራት / በኢኮኖሚ የተሻሉ ሀገራት ሄደው ሰርተው ፣ ጥሩ ገቢ አግኝተው ለራሳቸው ተርፈው ፤ ዋጋ ለከፈለላቸውና ተቸግሮ ላሳደጋቸው ቤተሰባቸው እንዲሁም ለህብረተሰባቸው መድረስ እና ' አለሁላችሁ ' ማለት ይፈልጋሉ።

እድሜ ቆሞ አይጠብቅምና ፈጣሪ በሰጣቸው የወጣትነት ጊዜ ጉልበትና እውቀታቸውን ተጠቅመው ቢያንስ እነሱ ባይደላቸው ለልጆቻቸው የሚሆን ነገር ማስቀረት ትልቁ ምኞታቸው ነው።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በወጣቱ ዘንድ ከሀገር ወጥቶ ለመስራት የሚታየው ፍላጎት እጅግ በጣም መጨመሩን በተለያየ መንገድ ለመገንዘብ ችሏል።

በተለይ ወደ ካናዳ፣ ጣልያን፣ አሜሪካ፣ ደቡብ አፍሪካ፣ ሳዑዲ፣ የተባበሩት አረብ ኤሜሬትስ፣ ሮማኒያ፣ ጀርመን፣ እንግሊዝ... ሌሎችም የውጭ ሀገራት በትምህርት እና በስራ ለመሄድ ፕሮሰስ የሚያደርጉ በርካታ ወጣቶችን ማነጋገር ችለናል። ሀሳባቸውንም ተቀብለናል።

አንድ ካናዳ ለመሄድ በዝግጅት ላይ ያለ ወጣት ፥ " እኔ ከዩኒቨርሲቲ በትልቅ ውጤት ከተመረቅኩ አንስቶ ባለፉት 3 ዓመታት ያልሞከርኩት የስራ ሙከራ የለም ባለሁበት አካባቢ አጠቃላይ የቅጥር ሁኔታ ተስፋ አስቆራጭ ሆኖብኝ በግሌ ለመንቀሳቀስ ሞክሬ አይደለም ህይወቴን ላሻሻል ዳግም የቤተሰብ እጅ ጠባቂ ሆኛለሁ " ሲል ገልጿል።

" በዚህም ምክንያት ከሰዎች ብር አፈላልጌ ወደ ውጭ ሀገር በመሄድ ያለውን ነገር ሁሉ ለመስራት እየጣርኩኝ ነው " ብሏል።

ሌላኛዋ ወጣት በተመሳሳይ የዩኒቨርሲቲ ምሩቅ ስትሆን " በተግባር የስራ እድል ማግኘት አስቸጋሪ እየሆነ ነው ፤ የሚሰራው በትውውቅ በብሄር እና በዝምድና ነው እንዴት ይሄንን ማለፍ እንዳለበኝ አላውቅም " ብላለች።

ለበርካታ ወራት እዚሁ ሀገር ውስጥ ሆኖ ሰርቶ ለመቀየር በሚል ብዙ ሙከራ ብታደርግም ስላልተሳካ የውጭ ሀገር እድል እየሞከረች እንደሆነ አመልክታለች።

ሌላኛው ቃሉን የሰጠ ክሩቤል የተባለ ወጣት ፥ ምንም እንኳን በስራ ላይ በሚገኝም በወር የሚያገኘው ገቢ አነስተኛ በመሆኑ በአጭር ጊዜ ትዳር ይዞ፣ የራሱን ሃሳብ አሳክቶ፣ ለቤተሰብ ፣ ለወገን ተርፎ መኖር የማይታሰብ ስለሆነበት ውጭ ሀገር ሰርቶ የመመለስ ፍላጎት እንዳለውና ይህን ለማድረግ እየሞከረ እንደሆነ ጠቁሟል።

ሌሎች ያናገርናቸው ወጣቶችም ባለው የኢኮኖሚ ሁኔታ ፣ ስራም ለማግኘት የሚያደርጉት ጥረት ተስፋ ስላስቆረጣቸው ውጭ ሀገር ለመሄድና ማንኛውም ስራ ለመስራት ሲሉ እድላቸውን እየሞከሩ እንደሆነ ተናግረዋል።

" ማንኛውም ሰው ሀገሩን ጥሎ የሚወጣው ሀገሩን ጠልቶ ሳይሆን የተሻለ ኑሮ ፍለጋ ነው " የሚሉት ወጣቶቹ በዚህ እድሜ ካልሰራን መቼ ልንሰራ ነው ? ሲሉ ጠይቀዋል።

ቃላቸውን የሰጡት ወጣቶች ፦
- በሀገር ውስጥ ያለው የስራ እድል እንዲሰፋ ፣
- በትውውቅ፣ በብሄር፣ በዝምድና የሚፈጸም ቅጥር እንዲቆም
- በገንዝብ የሚፈጸም ቅጥር እንዲቀር ካልተደረገ ወጣቱ እዚህ ሰርቶ የመለውጥ ተስፋው እንደሚሞት አስገንዝበዋል።

ሌላው " በሙስና የሚዘረፈው ብር ብዙ ነው እሱን ተከላክሎ ለወጣቶች አንዳች ነገር እንኳ ማድረግ ይቻላል ፤ ግን ዘራፊው የበለጠ ሃብቱን እያካበተ ወጣቱ የበለጠ ተስፋ እየቆረጠ ነው " ብለዋል።

አሁን ላይ በየመስኩ ሙስና መንሰራፋቱን ስራ ለመቀጠር፣ ጉዳይ ለመጨረስ እጅ መንሻ ካልተሰጠ እንደማይሆን በተግባር እንደተመለከቱ ጠቁመው ይሄ እያደር መዘዙ የከፋ ይሆናል ሲሉ አሳስበዋል።

" በሙስና በየአመቱ የሚዘረፈው የዚህች ሀገር ሃብት ለስንት ወጣቶች ህወይት መቀየሪያ ይበቃ ነበር ? " ሲሉም ጠይቀዋል።

ወጣቶች በሀገራቸው ላይ ሰርተው እንዲቀየሩ ምቹ ሁኔታ ከሌለ፣ እድሎችና ለስራ ለፈጠራ የሚሆን ሀቀኛ መደላደሎች ካልተፈጠሩ በሀገር ሰርቶ መቀየር አስቸጋሪ ስለሚሆን ሊታሰብበት ይገባል ብለዋል።

" ፖለቲከኞችም ሆኑ ለሀገር እናስባለን ተፅእኖ ፈጣሪ ነን የሚሉ ሰዎችም የወጣቶችን የኢኮኖሚ ጉዳይ አጀንዳ ሊያደርጉ ይገባል ዘውትር እነሱን የሚጠቅም ነገር ካልሆነ የመናገር እና ተፅእኖ የመፍጠር ፍላጎት የላቸውም " ሲሉ ተችተዋል።

(ቲክቫህ ኢትዮጵያ አ/አ)

#ቲክቫህኢትዮጵያ #የወጣቶችድምጽ

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
#SafaricomEthiopia

የሙዚቃ ኮከቦቹን በላይካችን ምርጥ 20 ውስጥ እናስገባቸው! 👏🏽 

እስከ መስከረም 20 ብቻ!

የዲጂታል ሙዚቃ ውድድርን ለመቀላቀል፡
🎥 የአንድ ደቂቃ የራሳችን ሙዚቃ ቪዲዮ በTikTok ላይ እንፖስት
🏷 #1Wedefit እና #የምትኖሩበትከተማ አድራሻ ማስገባት እንዳንረሳ
📲የTikTok ደረገጽ #Safaricomet ታግ እናድርግ

እንዝፈን! እንፖስት! እናሸንፍ!
መልካም ዕድል!

#1Wedefit #FurtherAheadTogether #DigitalMusicChallenge
ፎቶ፦ ከአዳማ ወደ ጂቡቲ የቁም እንስሳት የባቡር ትራንስፖርት አገልግሎት መጀመሩን የኢትዮ-ጅቡቲ ባቡር አክሲዮን ማኅበር ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር ታከለ ኡማ አስታውቀዋል፡፡

የባቡር ትራንስፖርት ከዚህ በፊት ወደ ሀገር ውስጥ ገቢ ምርቶችን ለማስገባት ብቻ የሚያገለግል ነበር።

የአገልግሎቱ መጀመር ወደ ውጭ ሀገራት ጥራት ያለውን የስጋ ምርት የመላክ አቅምን ይጨምራል ፤ የትራንስፖርት መጨናነቅን ይቀንሳል ብለዋል።

#Ethiopia #EngTakelUma

@tikvahethiopia