TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#Sidama

" በህዝብ ላይ ጉዳት እያደረሰና እያስመረረ የሚቀጥል አመራር አይኖርም " - አቶ አለማየሁ ጢሞቲዮስ

በሲዳማ ክልል የጸጥታ አካላት ግምገማ መደረጉን ተከትሎ በርካታ የፖሊስ አዛዥች ከስልጣን ሲነሱ በጥቂቶች  ላይ ከህገወጥ ንግድና ኮንትሮባንድ ጋር በተያያዘ ምርመራ እንደተጀመረባቸው ተሰምቷል።

ከሰሞኑ በክልሉ ሲካሄድ የሰነበተውን የግምገማና የውይይት መድረክ አሰመልክተው ንግግር ያደረጉት የክልሉ ሰላምና ጸጥታ ኃላፊዉ አቶ አለማየሁ ጢሞቲዎስ " በህዝብ ላይ ጉዳት እያደረሰና እያስመረረ የሚቀጥል አመራር አይኖርም " ብለዋል።

" በዚህ መሰረት በተደረገ ግምገማ በክልሉ በተለያዩ ዞን ወረዳና ከተማ አስተዳደር ውስጥ
ባሉ መዋቅር ይሰሩ ከነበሩ አመራሮች ውስጥ ሰባት የፖሊስ አዛዦችና ሙሉ የአንድ ክፍለ ከተማ የማኔጅመንት አባላት ላይ ከህገወጥ ንግድና ኮንትሮባንድ ጋር በተያያዘ ምርመራ እንዲጀመር ታዟል " ሲሉ ገልጸዋል።

ከኃላፊነታቸው እንዲነሱ ከተደረጉ አመራሮች መካከል ፦
- የምስራቃዊ ሲዳማ ዞን ፖሊስ መምሪያ ዋና አዛዥ፣
- የሆኮ ወረዳ ፖሊስ አዛዥ
- የጨቤ ወረዳ ፖሊስ አዛዥ ይገኙበታል።

የዳዬ ከተማ ፖሊስ አዛዥ ከኃላፊነታቸው ታግደው ከመልካም አስተዳደር ችግሮችና ከህገወጥ ንግድ ጋር ተያይዞ የተጠረጠሩባቸው ጉዳዮች እንዲጣራ ታዟል።

በተጨማሪም ደቡባዊ ሲዳማ ዞን ፖሊስ መምሪያ ዋና አዛዥ በዞኑ ህገ-ወጥ ንግድና የኮንትሮባንድ እንቅስቃሴ እየተበራከተ በመምጣቱና መቆጣጠር ባለመቻላቸው ከኃላፊነታቸው ሊነሱ ችለዋል።

በወረዳ ደረጃ ደግሞ የሁላ ወረዳ፣ የአለታ ጩኮ ወረዳ፣ የቡርሳ ወረዳና የጠጢቻ ወረዳ ፖሊስ አዛዦች የተነሳባቸው ጉዳዮች ተጣርቶ ውሳኔ እንዲሰጥበት አቅጣጫ ተቀምጧል።

በሀዋሳ ከተማ ምስራቅ ክፍለ ከተማ ያሉ ጠቅላላ ማኔጅመንቱ ከኃላፊነት እንዲነሱ መደረጋቸው ተነግሯል።

በመድረኩ በርካታ ችግሮች የተነሱ ሲሆን ለአብነትም ኪራይ ሰብሳቢነትና ባለጉዳይን ማማረር ጎልተዉ የተነሱ ክፍተቶች ናቸው።

#TikvahEthiopiaFamilyHW

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ለጥንቃቄ_ከጠቀማችሁ 1. በአዲስ አበባ ከተማ የሜትር ታክሲ አገልግሎት የምትሰጡ ወንድም እህቶቻችን እባካችሁ ጥንቃቄ አድርጉ። ማክሰኞ ምሽት 4 ሰዓት ገደማ ወደ ጎተራ ማሰለጫ መውረጃ ወይም በተቃራኒ ወደ ቄራ የሚወስደው መስቀለኛ መንገድ አካባቢ አንድ አገልግሎት ሰጪን 3 ተሳፋሪ መስለው የገቡ ወንበዴዎች መሃል አስፓልት ፣ በብዛት መኪና በሚመላለስበት መንገድ ላይ ከውስጥ እቃ ይዘው ሲሮጡ መመልከቱን…
#AddisAbaba

“ የጫት መቃሚያ ፣ የሺሻ ቤቶች የወንጀል ድርጊት የሚዶለትባቸው ቤቶች ናቸው ” - ፓሊስ

በአዲስ አበባ ከተማ የተለያዩ ወንጀሎች እንደሚደርሱባቸው ነዋሪዎች ይገልጻሉ፡፡

አንዳንዶቹ እንደሚሉት ከሆነ፣ የጸጥታ አካላት ልብስ ለብሰው ጸጥታ አስከባሪ በመምሰል ወንጀል የሚፈጽሙ አሉ።

ቲክቫህ ኢትዮጵያም ፦

°  ተመሳስለው ወንጀል የሚሰሩ አካላት ላይ ምን አይነት ክትትል እየተደረገ ነው ?

°  ወንጀል በከተማዋ በምን ደረጃ ይገኛል ?

° ሕዝቡ ምን አይነት ጥንቃቄ ማድረግ አለበት ? ሲል የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽንን ጠይቋል።

የኮሚሽኑ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ምክትል ኮማንደር ማርቆስ ታደሰ ምን አሉ ?

“ ሌባ የተለያዬ የወንጀል አፈጻጸም ስልት አለው፡፡ አንዱ የጸጥታ አካል መስሎ፣ ልብሱን በተለያዬ አይነት መንገድ ለማግኘት ሙከራ አድርጎና ለብሶ ወንጀል ሊፈጽም ይችላል፡፡

ይሄ በጣም ከበ ሁለት ጥፋት ነው፡፡

አንደኛው ህብረተሰቡ ፖሊስ ሊመስለው ከቻለ በፖሊስ ላይ ያለው አመኔታ ምንም ጥያቄ የለውም ይወርዳል፡፡ ሁለተኛው ጉዳት ደግሞ ወንጀሉ በፖሊስ ላይ ጫና/ሥራ ይፈጥራል፡፡

ስለዚህ ጥንቃቄ ማድረግና መረጃዎች በሚኖሩ ሰዓት ቶሎ መስጠት ያስፈልጋል፡፡

በተለይ በእንደዚህ አይነት ሁኔታዎች የሚፈጸሙ ወንጀሎች በጣም አደገኛ ናቸው፡፡ በጣም በጣም፡፡ ትልቅ ዋጋም የሚያስከፍሉ ናቸው፡፡

ወንጀል ፈጻሚውን በመያዛችን የጸጥታ አካላትን ልብስ ከየት አመጣህ ? ብሎ ለመጠየቅና ተባባሪ የሆነ አካል ካለ ተገቢ እርምጃ ለመውሰድ ምቹ ሁኔታ ይፈጥርልናል፡፡

ወንጀሉ ላይ ጠንካራ እርምጃ ለመውሰድና ለህዝብ ግልጽ በማድረግ በእንደዚህ አይነት ወንጀል የተሰማሩ ሰዎች ሁለት፣ ሦስቴ እንዲያስቡ እናደርጋለን፡፡

ግን ሰው መረጃ በመስጠት ተባባሪ መሆን መቻል አለበት፡፡

መረጃ ማድረስ ብቻ ሳይሆን ፈጣን ማድረስ ነው መሆን ያለበት፡፡ አንዳንድ ጊዜ አንዳንድ ሰዎች ሰው መክሯቸው ' መረጃ ስጡ ' ተብለው ነው የሚናገሩት፡፡ ፈጣን ነው መሆን ያለባቸው፤ እንደዚያ ከሆነ ወዲያው በቁጥጥር ሥር እናውላቸዋልን፡፡

ወንጀሎች ከመፈጸማቸው አስቀድሞ ለመፈጸሙ ምክንያት የሆኑ ነገሮችን አስቀድሞ በማወቅ የማስወገድ ሥራ መሰራት አለበት፡፡

ለምሳሌ ፦ የወንጀል መንስኤ ብለን እኛ የምናያቸው የጫት መቃሚያ፣ የሽሻ ቤቶች የወንጀል ድርጊት የሚዶለትባቸው ቤቶች ናቸው፡፡

በዚህ በኩል ፖሊስ የሚወስደው በጣም ጠንካራ የሆነ እርምጃ አለ፡፡ ግን መረጃ ከመስጠት በኩል አሁንም ክፍተቶች አሉ፡፡ አንዳንዶቹ እንዳውም ለፖሊስ መረጃ ከመስጠት ይልቅ የመደበቅ ሁኔታ አለ፡፡

ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር ሆነን ነው የወንጀል መከላከልን ሥራ የምንሰራው፡፡ ግን ግለሰቦቹ ወንጀል ከተፈጸመባቸው ወደ ሚዲያ ሳይሆን ወደ ፖሊስ ጣቢያ ነው መሄድ የሚጠበቅባቸው፡፡ በትክክል የከተማውን የጸጥታ ሁኔታ ቼክ የምናደርግበትም አግባብ ያ ነው፡፡

ስለዚህ ወንጀል ሰዎች ላይ ሊፈጸም ይችላል፡፡ በተቻለ አቅም በከተማው ላይ የወንጀል ስጋት እንዳይኖር ነው እየተሰራ ያለው፡፡ በ2016 ዓ/ም አጠቃላይ የተቋማችን አፈጻጸም 31 ፐርሰንት ወንጀልን ቀንሰናል፡፡

አዲስ አበባ ትልቅ ከተማ በመሆኗ ለተለያዩ ወንጀል መፈጸሞች ምክንያት የሆኑ ነገሮች ሊያጋጥሙ ይችላሉ፡፡ ከክልል ከተሞችም በብዛት ሰዎች ይመጣሉ፡፡ ሰው ሥራ፣ ቋሚ አድራሽ ከሌለው ያለው አማራጭ አንድም መለመን ካልሆነም ወደ ዘረፋ የሚገባበት ሁኔታ ይኖራል፡፡

አጠቃላይ የከተማውን ነባራዊ ሁኔታ ተቋቁመው ከግምት ውስጥ በማስገባት የወንጀል መከላከልን ሥራ በመስራት ከተማዋ የጸጥታ ሁኔታ ላይ እንድትሆን ማድረግ እጅግ በጣም ትልቅ ሥራ የሚጠይቅ ጉዳይ ነው፡፡

ከመደበኛ ሥራችን ጎን በጎን ኦፕሬሽናል የሆኑ ሥራዎችንም በመስራት በሌቦች ላይ ብቻ አይደለም በተቀባዮችም ጭምር ትልቅ ሥራ እየተሰራ ነው፤ በተለይ የመኪና እቃ ስርቆት በሚፈጽሙት፣ እቃውን በሚሸጡ፣ በሚደልሉ ላይ፡፡

በአዲስ ከተማና በልደታ ክፍለ ከተማ እንኳ በተሰራው ሥራ ወደ 71 ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ሥር አውለናል፡፡ እጅግ በርካታ ቁጥር ያለው የመኪና እቃም ይዘናል፡፡

ሆኖም በተለያዩ ቦታዎች ላይ ' ወንጀል ተፈጸመብኝ ' የሚል ሰው ሊያጋጥም ይችላል፡፡ እሱን ለመከላከል ደግሞ የምንሰራቸው ሥራዎች አሉ፡፡

ወንጀል የሚፈጽማባቸው አካላት ወደ ፖሊስ መጥተው ያመልክቱ፡፡ በርካታው ሰው ከዚያ ይልቅ ወደ ሚዲያ ይሄዳል፡፡ ወደ ሚዲያ አይሂድ ማለት አይደለም ግን ወደ ፖሊስ ቢመጣ ያለንበት የመከላከል አቅም የቱ ጋ ድርሷል ለማለት ይረዳናል።
"

#TikvahEthiopiaFamilyAA
#AddisAbabaPolice

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የአቪዬሸን አሰራርን በጣሰ መንገድ ግርግር እና ወከባ ፈጥረዋል ተብለው በቁጥጥር ስር የዋሉት 6 ተጠርጣሪዎች ዛሬ ለሁለተኛ ጊዜ ፍርድ ቤት ቀርበዋል። የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ተረኛ ችሎት የፌዴራል ፖሊስ የጠየቀውን የ14 ቀን የግዜ ቀጠሮ ፈቅዷል። ተጠርጣሪዎቹ የዋስትና መብት እንዲፈቀድላቸው በጠበቆቻቸው አማካኝነት ጠይቀዋል። ፍርድ ቤቱ ጥያቄውን ውድቅ አድርጓል። የፖሊስን የምርመራ…
#Update

ፍ/ቤት የክስ መመስረቻ ጊዜ ፈቀደ።

" የኢትዮጵያ አየር መንገድን ደህንነት አደጋ ላይ ለመጣል ተንቀሳቅሰዋል ፤ የአቪዬሸን አሰራርን በጣሰ መንገድ ግርግር እና ወከባ ፈጥረዋል " ተብለው የተጠረጠሩ 6 ግለሰቦች ላይ የፌዴራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ ተረኛ ጊዜ ቀጠሮ ችሎት ክስ መመስረቻ ጊዜ መፍቀዱ ተሰማ።

የፌደራል መርማሪ ፖሊስ የምርመራ ቡድን፦
- ዮሃንስ ዳንኤል
- አማኑኤል መውጫ፣
- ናትናኤል ወንድወሰን፣
- ኤልያስ ድሪባ፣
- ይዲድያ ነጻነት እና እሌኒ ክንፈ በተባሉ ግለሰቦች ላይ ሲያከናውን የቆየውን የምርመራ ማጣሪያ ስራ አጠናቆ መዝገቡን ለዐቃቤ ሕግ ማስረከቡን አስታውቋል።

የፍትህ ሚኒስቴር የተደራጁና ድንበር ተሻጋሪ ጉዳዮች ዐቃቤ ህግ በችሎት ተሰይሞ የምርመራ መዝገቡን ከፖሊስ ጳጉሜን 1 ቀን 2016 ዓ.ም መረከቡን ጠቅሶ፤ ማስረጃ ተመልክቶ ክስ ለማቅረብ እንዲያስችለው ክስ ለመመስረቻ ጊዜ 5 ቀን እንዲሰጠው ጠይቋል።

የተጠርጣሪዎቹ ጠበቆች " ዐቃቤ ህግ ምርመራውን ሲመራ ቆይቶ እንደአዲስ መዝገቡን ተመልክቼ ክስ ለመመስረት፣ ለመወሰን እንዲያስችለኝ የክስ መመስረቻ ጊዜ ይሰጠኝ ማለቱ " ተገቢ አይደለም በማለት ተከራክረዋል።

ጠበቆቻቸው ደንበኞቻቸው ተጨማሪ ጊዜ በእስር ሊቆዩ እንደማይገባ ገልጸው፤ የዋስ መብታቸው እንዲከበር ጠይቀዋል።

የግራ ቀኝ ክርክሩን የመረመረው ጊዜ ቀጠሮ ችሎቱ ዐቃቤ ህግ ክስ የመመስረቻ ጊዜ መፍቀድ ስነ ስርዓታዊ መሆኑን በማመን የተጠርጣሪዎችን የዋስትና ጥያቄ በማለፍ ለዐቃቤ ህግ የ5 ቀን የክስ መመስረቻ ጊዜ መፍቀዱን ኤፍ ቢ ሲ ዘግቧል።

በዚህም መስከረም 3 ቀን 2017 ዓ/ም ክስ ይመሰረታል።

@tikvahethiopia
#Tigray

ባጋጠመ አሰቃቂ የትራፊክ አደጋ ከ10 በላይ ተሳፋሪዎች ህይወታቸው ተቀጠፈ።

የትራፊክ አደጋው ዛሬ  ጳጉሜን 4/2016 ዓ.ም ከቀኑ 5:00 ሰዓት አከባቢ የተከሰተ ሲሆን የሰሌዳ ቁጥር TG - 04539 የሆነ መለስተኛ የህዝብ ማመላለሻ አውቶቡስ ከዓድዋ ወደ መቐለ ሲጓዝ ወርዒ ልዩ ቦታ  እንዳፈላሲ ቁልቁለት ሲወርድ ወደ ገደል በመግባቱ ነው አደጋው ያጋጠመው።

በውስጥ ከተሳፈሩ ሰዎች ከ10 በላይ ወድያውኑ ህይወታቸው ሲያልፍ 5 ሰዎች በፅኑ ተጎድተዋል።

ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ የደረሰው መረጃ እንደሚያመላክተው 48 ሰዎች የመጫን አቅም ያለው መለስተኛ አውቶቡስ በአጋጣሚ 20 ሰዎች ብቻ አሳፍሮ መጓዙ ለሟችና ቁስለኞች መቀነስ ምክንያት ሆኗል።

የአደጋው ምክንያት ገና በመጣራት ላይ ነው።

ይህ ወር በርካታ በዓላት የሚከበሩበት በመሆኑ ብዙ የትራፊክ እንቅስቃሴ ይኖራል ፤ በመላው ኢትዮጵያ የምትገኙ አሽከርካሪዎች ጥንቃቄ አይለያችሁ።

#TikvahEthiopiaMekelle

@tikvahethiopia 
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ውጤት : የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት ዛሬ ይገለጻል።

የትምህርት ሚኒስቴር በውጤቱ ዙሪያ ከደቂቃዎች በኃላ መግለጫ ይሰጣል።

መግለጫውን ቲክቫህ ኢትዮጵያ በቀጥታ የሚያሰራጭ ይሆናል።

ይጠብቁ !

#TikvahEthiopiaFamilyAddisAbaba

@tikvahethiopia
Live stream scheduled for
Live stream started
TIKVAH-ETHIOPIA
#ውጤት : የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት ዛሬ ይገለጻል። የትምህርት ሚኒስቴር በውጤቱ ዙሪያ ከደቂቃዎች በኃላ መግለጫ ይሰጣል። መግለጫውን ቲክቫህ ኢትዮጵያ በቀጥታ የሚያሰራጭ ይሆናል። ይጠብቁ ! #TikvahEthiopiaFamilyAddisAbaba @tikvahethiopia
#ውጤት : የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት ዙሪያ መግለጫ እየሰጡ ይገኛሉ።

ሚኒስትሩ የፈተናው ውጤት ለሊት 6 ሰዓት ላይ ይፋ ይደረጋል ብለዋል።

መግለጫውን ከላይ በቀጥታ ይከታተሉ።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
አጠቃላይ ፈተናውን ያለፉ ተማሪዎች 5.4 በመቶ ናቸው። @tikvahethiopia
ዘንድሮ ብሔራዊ ፈተና ከተፈተኑት ተማሪዎች 36,409 ተማሪዎች ናቸው ያለፉት።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ዘንድሮ ብሔራዊ ፈተና ከተፈተኑት ተማሪዎች 36,409 ተማሪዎች ናቸው ያለፉት። @tikvahethiopia
አዲስ አበባ 10,690 ተማሪዎች በማሳለፍ ከፍተኛውን ስፍራ ይዟል።

አዲስ አበባ ካስፈተናቸው ተማሪዎች 21.4 በመቶ አሳልፏል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
አዲስ አበባ 10,690 ተማሪዎች በማሳለፍ ከፍተኛውን ስፍራ ይዟል። አዲስ አበባ ካስፈተናቸው ተማሪዎች 21.4 በመቶ አሳልፏል። @tikvahethiopia
ከፍተኛ ውጤት ስንት ተመዘገበ ?

በሀገር ደረጃ ከፍተኛ ውጤት የተመዘገበው በትግራይ ነው።

በትግራይ ፈተናው ከ700 ነው የተሰጠው።

ከቀላሚኖ 675 ከፍተኛ ውጤት ተመዝግቧል ፤ በወንድ ተማሪ። ኢትዮጵያ ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው ተብሏል ከ700 ይሄን ያህል ውጤት ሲመዘገብ።

ሌላ በሀገር ደረጃ ከ600 ከተፈተኑት ውስጥ 575 ከፍተኛው ነው ከተፈጥሮ ሳይንስ ፤ የካቴድራል ተማሪ ናት።

ከማህበራዊ ሳይንስ 538 ተመዝግቧል። ከኢትዮ ፓረንትስ ትምህርት ቤት ናት።

በተፈጥሮም በማህበራዊ ሳይንስም ትልቅ ውጤት የመጣው በሴቶች ነው።

@tikvahethiopia
Live stream finished (55 minutes)
ሬሜዲያል ዘንድሮም ይኖራል።

" አምና ሰጥተናል። ዘንድሮ ከዓምናው የቀነሰ ቁጥር እንወስዳለን። የሬሜዲያል ፕሮግራም በሂደት እየቀነሰ ይሄዳል " ሲሉ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ተግረዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ሬሜዲያል ዘንድሮም ይኖራል። " አምና ሰጥተናል። ዘንድሮ ከዓምናው የቀነሰ ቁጥር እንወስዳለን። የሬሜዲያል ፕሮግራም በሂደት እየቀነሰ ይሄዳል " ሲሉ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ተግረዋል። @tikvahethiopia
#Amhara

የትምህርት ሚኒስቴር ፤ " ዘንድሮ ሁሉም
ክልሎች አምና ካሳለፉት ተማሪ በላይ አሳልፈዋል " ብሏል።

" በፐርሰንቴጅም በአክቹዋል ቁጥርም ካለፈው የተሻለ ነው " ተብሏል።

ከአክቹዋል ቁጥር ያነሰው አንድ ክልል ነው እሱም የአማራ ክልል እንደሆነ ተገልጿል።

ክልሉ ያነሰው ደግሞ የተፈተኑት ተማሪዎች ቁጥር ከግማሽ በታች ስለነበር ነው ተብሏል።

ክልሉ ፈተና ካስፈተናቸው ውስጥ ግን 6.6 በመቶ ተማሪዎች አልፈዋል።

አምና ከተመዘገበው 4.1 በመቶ ዘንድሮ በልጧል።

@tikvahethiopia
#Ethiopia

ውጤቱ በጣም ዝቅተኛ ነው !

" በ2016 ትምህርት ዘመን በወረቀትና በበይነ መረብ የተሰጠው ፈተና ውጤት እንድምታው ሲታይ ከ2014 ዓ/ም 30,034 (3.3%) ፣ ከ2015 ዓ/ም 27,267 (3.2%) ... (ዘንድሮ 5.4%) መሆኑ እያሽቆለቆለ እየሄደ ያለው ጉዞ የተገታ እና መጠነኛ የመሻሻል አዝማሚያ ያሳየ ቢሆንም አሁንም 50% እና ከዚያ በላይ ውጤት ያስመዘገቡ ተፈታኞች ቁጥር በጣም #ዝቅተኛ ነው። " - ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ (የትምህርት ሚኒስትር)

@tikvahethiopia