TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
አቶ ዓምዶም ገብረስላሴ የዓረና ሊቀመንበር ሆኑ።

የዓረና ትግራይ ለዴሞክራሲ እና ሉዓላዊነት ፓርቲ (ዓረና) ባካሄደው  5ኛ መደበኛ ድርጅታዊ ጉባኤ አቶ ዓምዶም ገብረስላሴን ሊቀ መንበር አድርጎ መርጧል።

አቶ ካሕሳይ ዘገየ ደግሞ የፓርቲው ምክትል ሊቀ መንበር ሁነው እንዲያገለግሉ መመረጣቸው ተነግሯል።

Via Abrha Desta

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
በትግራይ የኤሌክትሪክ ኃይል ለምን ተቋረጠ ? የኤሌክትሪክ ኃይል አገልግሎት ከነሃሴ 21 /2015 ዓ.ም ሌሊት ጀምሮ በመላ ትግራይ መቋረጡ ተገልጿል። ከኢትዮጵያ መብራት ኃይል አገልግሎት ትግራይ ቅርንጫፍ በተገኘው መረጃ መሰረት አገልግሎቱ የተቋረጠው በመኾኒ ባጋጠመ የመስመር መቋረጥ ነው። ችግሩን ዛሬ እስከ ቀኑ 10:00 ድረስ ለመፍታት አስቀደመው ወደ ተላኩ ባለሙያዎች ተጨማሪ የሰው ኃይል መላኩን…
#Update

መቐለ ጨምሮ በመላ ትግራይ ከነሃሴ 21 ሌሊት ጀምሮ  የኤሌክትሪክ ሃይል አገልግሎት መቋረጡ ይታወቃል።

በመቐለ ከተማ ዛሬ ነሃሴ 22/ 2015 ዓ.ም ከቀኑ 11:00 ጀምሮ የኤሌክትሪክ ኃይል አገልግሎት መሰጠት ጀምሮ አንድ ሰዓት ሳይሞላ ከፊሉ የከተማው አከባቢ ጠፍቶ ከፊሉ አገልግሎቱ በማግኘት ላይ መሆኑ የቲክቫህ መቐለ ቤተሰብ መረጃ አድርሶናል።

የኤሌክትሪክ ሃይል አገልግሎት ከነሃሴ 21 ሌሊት ጀምሮ በመላ ትግራይ የተቋረጠው መኾኒ ላይ ባጋጠመ የመስመር ችግር መሆኑን የኢትዮጵያ መብራት ኃይል አገልግሎት ትግራይ ቅርንጫፍ ማሳወቁ ይታወቃል።

ችግሩን ለመፍታት ርብርብር እየተደረገ እንደሆነ ተነግሯል።

ፎቶ ፦ ፋይል

@tikvahethiopia
#AddisAbaba

በአዲስ አበባ ለሚገኙ የኤሌክትሪክ ሞተር ሳይክል አሽከርካሪዎች ማስጠንቀቂያ ተሰጠ።

የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ ፤ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የሞተር ሳይክል አሽከርካሪዎችና ባለንብረቶች የኤሌክትሪክ ሞተር ሳይክል ነው በሚል በአዋጁ የተቀመጡ ዝርዝር መስፈርቶችን ማለትም ፦
- 3ኛ ወገን፣
- መድን ሽፋን ሰሌዳ፣
- ለተሽከርካሪው የሚመጥን መንጃ ፍቃድና
- ሌሎች በተሽከርካሪ መለያ፣ መመርመሪያና መመዝገቢያ አዋጅ ቁጥር 681/2002 የተዘረዘሩ አስፈላጊ መረጃዎች ሳያሟሉና የቴክኒክ ብቃታቸው ሳይረጋገጥ በከተማዋ እየተንቀሳቀሱ መሆኑን ደርሼበታለሁ ብሏል።

ከዛሬ ጀምሮ ግን በከተማዋ ያሉ የኤሌክተሪክ ሞተር ሳይክሎች በተሽከርካሪ መለያ፣ መመርመሪያና መመዝገቢያ አዋጅ ቁጥር 681/2002 ላይ በተቀመጠው መሰረት በሰዓት ከ20 ኪ.ሜ በላይ የሚንቀሳቀሱ ማንኛውም ተሽከርካሪዎችና ሞተር ሳይክሎች ላይ ይህንን አሰራር እንዲተገብሩ ሲል ቢሮው አሳስቧል።

ይህንን በማይፈፅሙና መስፈርቱን ሳያሟሉ በሚንቀሳቀሱ አሽከርካሪዎችና ባለንብረቶች ላይ ቢሮው ህጋዊ እርምጃ እንደሚወስድ አስጠንቅቋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" ኑሮውን አልቻለነውም " እጅግ በርካታ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት በየአካባቢያቸው የዳቦና የእንጀራ ዋጋ አሁን ላይ የደረሰበትን ጠቁመዋል። ከአዲስ አበባ ውጭ በክልል ከተሞች አንድ ትንሽ ተብሎ የሚታሰበው ዳቦ ከ5 ብር - 9 ብር ድረስ እንደየአካባቢው የሚሸጥ ሲሆን እንጀራ ከ15-20 ብር ድረስ ይሸጣል ፤ የፀጥታ ችግር ባለባቸው ቀጠናዎች ዋጋው እጅግ ተለዋዋጭ መሆኑን የገለፁት ቤተሰቦቻችን…
#ኢትዮጵያ

ዛሬ ጥዋት ከ #ዳቦ እና #እንጀራ ዋጋ በየጊዜው መጨመር ጋር በተያያዘ እንዲሁም በአጠቃላይ የኑሮው ሁኔታ ምን ያህል እየከበደ እንደሄደ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት ሃሳብ ሲያጋሩ ነበር።

ከእነዚህም ቤተሰቦች መካከል በጤና ባለሞያነት የምታገለግል የቲክቫህ ቤተሰብ አባል እኔ የምናገርበትን አጥቻለሁ ፤ የቲክቫህ ቤተሰቦች እየገፋው ያለሁትን ኑሮ ይስሙኝ ስትል መልዕክቷን እንዲህ ስትል ልካለች።

የጤና ባለሞያዋ የቲክቫህ አባል ፦

" እውነቱን ለመናገር ኑሮ ጫናዉ እኛ የመንግስት ሰራተኞች ላይ እጅጉን ብሷል።

ለምሳሌ ፦ እኔ በአንድ ትልቅ የመንግስት ሆስፒታል ውስጥ በፅኑ ህሙማን ክፍል ውስጥ እሰራሁ ደሞዜ 6193 ብር  የግብር ተቀንሶበት 4776 ብር ይደሳል።

Duty ተብሎ ሌሊቱን ሙሉ ከፅኑ ታካሚ ጋር ስለፋ አድሬ ጠዋት የታካሚውን የአዳር ሁኔታ የሚረከበኝ የቀን ተረኛ ከመጀመሪያው እስከ መጨረሻው አስረድቼና አስረክቤ ፤ ታዲያ የአደሩን ነገር አትጠይቁኝ መድሀኒት መስጠቱ ፣ በየ1 ሰዓቱ Vital ማንሳቱ ዳይፐር አንሶላ እንዲሁም ቁስል ማጠቡ እሄን ሁሉ አስረክቤ በከተማ አውቶብስ ድፍን ሁለት ሰዓት ወደሚፈጀው የተከራየሁት ቤት እጓዛለሁ።

የምስራበት አካባቢ ላይ እንዳልከራይ የደመወዜን እጥፍ ከየት አምጥቼ እከፍላለሁ ፤ ለዚህ ነው ከከተማ ወጥቼ የተከራየሁት እናማ ከመድከሜ የተነሳ አውቶብስ ላይ ማንቀላፉቱ የማይቀር ነው ፤ ቤት እደርስና የሚበላ ስለማይኖር ከምስራ ብተኛ ብዬ እተኛለሁ። 

እደዛ ወገቤ ተሰብሮ ዝዬ ፤ ሌላ ተጨማሪ ስራ እንዳልሰራ ደካክሜ ብቻ ምን አለፋችሁ ፤ ለዚህ ሁሉ ድካም ያቺ ደሞዝ ናት ያለችኝ  የDuty ክፍያ ተጨምራ እጄ ላይ የምትደርሰውን ብር ለቤት ክራይ ከፍዬ፣  የትራንስፖርት እና አስቤዛ አውጥቼ የት ትድረስና ? የኑሮው ጫና እኛ ላይ የባሰ ነው። "
.
.

ዛሬ አስተያየታቸውን ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የላኩ ዜጎች በኑሮ ውድነት ክፉኛ እየተፈተኑ መሆኑን በመግለፅ ፤ ገበያው በየጊዜው እየናረ ከዘላቂ መፍትሄ ይልቅ ሰሞነኛ ጉዳይ ሆኖ እያለፈ ነው ብለዋል።

ሚዲያዎችም ትኩረት የሚስብላቸው እና ገንዘብ የሚሰሩበት የፖለቲካ ፍጅትና ጦርነት ፣ ግጭት ስለሆነ ዜጎች እየተፈተኑበት ስላለው የኑሮ ውድነት ጉዳይ አድምተው ለመስራትና የሚመለከታቸውን አካላት ለመጠየቅ እንዲሁም መፍትሄ እንዲሰጥ ለመጋፈጥ ፍላጎት የላቸውም በማለት ወቅሰዋል።

ከድሃ ጎሮሮ ላይ እየነጠቁ የሚበለፅጉ አካላትም ፣ የራሳቸውን የኑሮ ምቾት ብቻ እያሰቡ የሚሯሯጡ ነጋዴዎችም ለአፍታ ለታችኛውና ኑሮ እየፈተነው ላለው ማህበረሰብ እንዲያስቡ ጠየቀዋል።

መንግሥትም ጆሮ ሰጥቶ የሚሰማ ከሆነ ዜጎች በኑሮ ውድነት በተለይም ደግሞ በምግብ ነክ ነገሮች ላይ በየጊዜው በሚደረገው ጭማሪ ዜጎች እየተሰቃዩነውና መፍትሄ ይፈልግ ብለዋል።

Via @tikvahethiopiaBOT

@tikvahethiopia
Jasiri is a regional hub, dedicated to driving development in the wider East African area.

We carefully select candidates from Ethiopia, Rwanda, and Kenya to take part in our programs, which are designed to make a meaningful contribution to the African Union's vision of a progressive, dynamic, and united Africa.

Application to join our Cohort 5 is ongoing, apply today at http://jasiri.org/application

#Jasiri4Africa
ወደ *777# በመደወል የሳፋሪኮምን ዕለታዊ የዩቲዩብ ጥቅሎች እንግዛ ፣ አዳዲስ ዕውቀቶችን እንቅሰም!

#SafaricomEthiopia #FurtherAheadTogether
ብቋንቋ ትግርኛ ሓበሬታታት : ጥቆማን ሓሳባትን ንለዋወጠሉ መድረኽ ተኸፊቱ ኣሎ።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ / ትግርኛ https://publielectoral.lat/TikvahEthiopiaTigrigna

ምክትታልኩምን ሓበሬታኹምን ኣይፈለየና።
" በውጭ ሀገራት መጽሐፍትን ማሳተሙ በሀገር ኢኮኖሚ ላይ ጉዳት ይስከትላል " - የትምህርት መሣሪያዎች ማምረቻና ማከፋፈያ ድርጅት

በዓመት 10 ሚሊዮን የትምህርት መጽሐፍትን የማተም አቅም ቢኖረውም በርካታ ክልሎች መጽሐፍትን በውጭ ሀገራት እያሳተሙ መሆኑን የ " ትምህርት መሣሪያዎች ማምረቻና ማከፋፈያ ድርጅት " አስታወቀ።

የክልልና የከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮዎች በበኩላቸው በጨረታ ሀገር ውስጥ እያሳተሙ መሆኑን አሳውቀዋል።

ድርጅቱ ምን አለ ?

የመማሪያና የማስተማሪያ መጽሐፍትን ማተም አንዱ የድርጅቱ ተግባር መሆኑን ገልጾ በክልሎች የሚመጣው ጥያቄ አነስተኛ በመሆኑ ድርጅቱ ባለው አቅም ልክ እየሠራ እንዳልሆነ ገልጿል።

የተወሰኑ ክልሎች የትምህርት መጽሐፍትን በድርጅቱ በማሳተም እየተጠቀሙ ሲሆን የበርካታ ትምህርት ቢሮዎችና ትምህርት ሚኒስቴር ግን በሀገር ውስጥ ሕትመቱን ከማከናወን ይልቅ በውጭ ሀገራት የውጭ ምንዛሬ በመክፈል ማሳተምን ምርጫቸው ማድረጋቸው የድርጅቱ ውጤታማነት ላይ ጫና እያሳደረበት ገልጿል።

ድርጅቱ ትምህርት ሚኒስቴርና ትምህርት ቢሮዎች የመጽሐፍት ሕትመት ጨረታ በሚያወጡበት ወቅት ጨረታዎችን የሚያሸንፋቸው ጊዜያት መኖራቸውን አመልክቶ ነገር ግን በክልሎች ፍላጎት ማጣት የተነሳ በጋራ የመሥራት ልምዱ የለም ብሏል።

የትምህርት መማሪያ መጻሕፍት እንዲሁም የተለያዩ ግብዓቶችን ለማምረት በቂ ዝግጁነት እዚሁ እያለ በውጭ ሀገራት መጽሐፍትን ማሳተሙ በሀገር ኢኮኖሚ ላይ ጉዳት የሚስከትል መሆኑን መገንዘብ አለባቸውም ብሏል።

ክልሎች ለመማሪያ መጽሐፍት ሕትመት ወደውጭ ከመሄድ ይልቅ በሀገር ውስጥ ድርጅቶች ቢያሳትሙ የተለያዩ ወጪዎችን መቀነስ እንደሚችሉ ድርጅቱ ገልጿል።

ድርጅቱ በዓመት የ10 ሚሊዮን መጽሐፍ ኮፒዎችን የማምረት አቅም ቢኖረውም በ2015 ዓ.ም አገልግሎቱን ፈልገው ለመጡ ለአማራ ክልል በከፊል፣ ለሐረሪ ክልል፣ ለሶማሌ ክልልና ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮዎች 3 ሚሊዮን መጽሐፍትን ብቻ አሳትሟል።

ሌሎቹ ሕትመቱን በውጭ ማከናወን የፈለጉ ክልሎች ከዋጋ ውድነቱ በተጨማሪ ከወደብ ለማጓጓዝ የሚወስድባቸው ጊዜ ከፍ እንዳለባቸው ድርጅቱ ጠቁሟል።

እንደሀገር እየተነሳ ላለው የመማሪያ መጽሐፍት እጥረት ዋና መንስኤ ወደድርጅቱ የሚመጡ የሕትመት ጥያቄዎች አነስተኛ መሆናቸው ነውም ብሏል።

ትምህርት ቢሮዎች ምን ይላሉ ?

የአፋር ትምህርት ቢሮ ፤ በ2015 በጀት ዓመት የ7ኛና የ8ኛ ክፍል የመጽሐፍት ሕትመትን ሀገር ውስጥ በሚገኘው በሜልባ ፕሪንቲንግ፣ ፐብልሽንግና ፓኬጂንግ አክሲዮን ማኅበር እንዳሳተመ ገልጸዋል።

ለ2016 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ከ1ኛ እስከ 6ኛ ክፍል የሚያስፈልጉ የመማሪያ መጽሐፍት በዚሁ የሕትመት ድርጅት አማካኝነት እየተዘጋጁ ነው ብሏል።

የድሬዳዋ ትምህርት ቢሮ ፤ በበኩሉ ባወጣው ጨረታ መሠረት ሕግና ሥርዓትን ተከትሎ የመጽሐፍት ሕትመት እንደሚከናወን ገልጿል።

አነስተኛ ዋጋ ያቀረበውና ጨረታውን ያሸነፈው " ሜልባ የሕትመት ድርጅት " በመሆኑ የመማሪያ መጽሐፍቱን አሳትሟል ሲል ገልጿል።

የሕትመት ጨረታ በሚያወጣበት ወቅት ማንኛውም አቅም ያለው የሀገር ውስጥ ሕትመት ድርጅት መወዳደር የሚችልበት አሠራር እንዳለ አሳውቋል።

#MOE - ከ9ኛ እስከ 12ኛ ክፍል የሚያስፈልጉ የመማሪያ መጽሐፍትን የማቅረብ ኃላፊነት ያለበት የትምህርት ሚኒስቴር የመጽሐፍት ሕትመቱን በብዛት የሚያከናውነው በውጭ ሀገራት ነው።

ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት

@tikvahethiopia
#WolaitaSodo

ከጥቂት ቀናቶች በፊት በአርባምንጭ ከተማ የምስረታ ጉባኤውን ያደረገው የ " ደቡብ ኢትዮጵያ ክልል  መንግስት " ዛሬ የሥራ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ያካሂዳል።

የፌዴሬሽኑ 12ኛው ክልል የስራ ማስጀመሪያውን መርሀግብር የሚያከናውነው በዛሬው ዕለት በዎላይታ ሶዶ ከተማ ነው።

ከተማዋም ባለፉት ሳምንታት አዲሱን የክልሉን አመራር አቀባበል ለማድረግ ዝግጅቷን ስታካሂድ ነበር።

ዛሬ ለሚካሄደው የስራ ማስጀመሪያ መርሀግብር የፌዴራልና የአዲሱ ክልል ከፍተኛ አመራሮች ወደ ከተማው ገብተዋል።

በአዲሱ አደረጃጀት የተቋማት ክፍፍል መሰረት " ዎላይታ ሶዶ " የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳደር ዋና መቀመጫ እንዲሁም የክልሉ ዋና የፖለቲካ ማዕከል ናት።

ፎቶ፦ የዎላይታ ዞን ኮሚኒኬሽን

@tikvahethiopia
#USA

የአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ ልዑክ ማይክ ሐመር ከነሐሴ 22 እስከ ጳጉሜ 3 ድረስ በኬንያ  እና በኢትዮጵያ ቆይታ እንደሚያደርጉ የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አሳውቋል።

በናይኖቢ እንዲሁም በአዲስ አበባ ቆይታቸው ከሀገራቱ ባለስልጣናት፣ ከአፍሪካ ህብረት፣ ከልማት ድርጅት ባለስልጣን እና ሌሎች ዓለም አቀፍ አጋሮች ጋር ይነጋገራሉ ተብሏል።

ሐመር በአዲስ አበባ በሚያደርጉት ቆይታ፣ በአማራና ኦሮሚያ ክልሎች ያሉትን ግጭቶች በድርድር እንዲቋጩ እና ሰላማዊ ሰዎች ላይ ጥቃት እንዳይደርስ እና ከለላ እንዲያገኙ ግፊት ያደርጋሉ ተብሏል።

ሐመር፣ በሱዳን ቀውስ እና ጦርነቱን ለማስቆም እየተደረጉ በሚገኙ ቀጠናዊና ዓለማቀፋዊ ጥረቶች ላይም ከአካባቢዉ አገራት፤ ከአፍሪቃ ኅብረትና ከኢጋድ መሪዎች ጋር እንደሚመክሩ የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ገልጿል።

የአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ማይክ ሐመድ ከዚህ ቀደም በተለይም በትግራይ ከነስቶ ወደ አፋር እና አማራ ክልል የተስፋፋውን የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ሰላማዊ መፍትሄ እንዲበጅለት በተደጋጋሚ ወደ ኢትዮጵያ እና ጎረቤት ሀገራት መምጣታቸው የሚዘነጋ አይደለም።

@tikvahethiopia