TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ሻሸመኔ

ዛሬ በሻሸመኔ ከተማ ቆሻሻ ውስጥ ተጥሎ የነበረ ቦምብ ፈንድቶ ያገለገሉ ፕላስቲኮችን እየለቀሙ የሚተዳደሩ አራት ልጆች ህይወታቸው አለፈ፡፡

ልጆቹ ያገለገሉ ፕላስቲኮችን እየለቀሙ ባለበት ሰዓት ከተጠራቀመ ቆሻሻ ውስጥ ቦምቡ መፈንዳቱን ፖሊስ ገልጿል።

በዚህም የአራት ልጆች ህይወታቸው ሲያልፍ፥ ሁለት ህፃናት ጉዳት ደርሶባቸዋል፡፡

Via OBN / FBC

@tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#EthioOnlineMarket

የነዚህ ማጠቢያ ማሽኖች ዋጋ ፤ የብዙ ነገሮችን ጨዋታ ቀይሯል! ዋጋቸውን ለማየ : https://publielectoral.lat/EOMMarket

- የመረጡትን እቃ ይዘዙን፤ያሉበት ድረስ በነፃ  እናደርሳለን : 𝗣𝗵𝗼𝗻𝗲  ☞0929181818 / 0909868788

ይምጡ የሽያጭ ማእከሎቻችን ይጎብኙ፤ ተደስተው ይመለሳሉ !
አድራሻችን፦
• ቁጥር 1:- መገናኛ, ቤተልሄም ፕላዛ  የሱቅ
                 ቁጥር  G-10 ግራውንድ 
•ቁጥር 2:- ሜክሲኮ, ኬኬር ህንፃ የሱቅ  
                ቁጥር #338
•ቁጥር 3:- አያት አደባባይ , AAT CITY   
                  CENTER G-11 ግራውንድ
𝕵𝖔𝖎𝖓 𝖔𝖚𝖗 𝖈𝖍𝖆𝖓𝖓𝖊𝖑 @EOMmarket
            
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update

ዛሬ በዎላይታ ዞን ሲካሄድ የዋለው ያድጋሜ የሕዝበ ውሳኔ ምርጫ ድምጽ አሰጣጥ ሒድት መጠናቀቁ ተገልጿል።

አሁን ላይ በየምርጫ ጣቢያዎቹ የድምጽ ቆጠራ እየተከናወነ  እንደሚገኝ ተነግሯል።

በነገው ዕለት ማለዳ የቆጠራው ውጤት ለሕዝቡ ይፋ ይደረጋል ተብሎ ይጠበቃል።

በየምርጫ ጣቢያዎቹ የሕዝብ ፍሰት በመኖሩ የድምጽ አሰጣጥ ሒደቱ እስከ ምሽቱ አንድ ሰዓት ተራዝሞ መጠናቀቁን ብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ዋቢ በማድረግ ኤፍ ቢ ሲ ዘግቧል።

ፎቶ ፦ NEBE

@tikvahethiopia
የወልቃይት ጉዳይ !

ኮሌኔል ደመቀ ዘውዱ ከቢቢሲ አማርኛው አገልግሎት ጋር ሰፋ ያለ ቃለ ምልልስ አድርገዋል።

በዚህ ቃለምልላሳቸው ፦

- ስለ ማንነት ጥያቄ
- ስለ በጀት
- ስለ ተጠያቂነት
- ስለ ተፈናቃዮች ጉዳይ
- በእሳቸው ላይ ስለሚቀርቡ ክሶች
- ስለ ፖለቲካ ውሳኔ / ህዝበ ውሳኔ
- ስለ ውይይት ጉዳዮች ተነስቶላቸው ምላሽ ሰጥተዋል።

ኮሌኔል ደመቀ ዘውዱ ምን አሉ ?

የማንነት ጉዳይ ፦

" እኛ የእናት ቋንቋችን አማርኛ ነው፣ ባሕላችን አማራ ነው ፤ ሥነ ልቦናችን የጎንደር ማኅበረሰብ ነው።

ስለዚህ ታሪካችን እና ማንነታችን ከጎንደር ጋር እንጂ ከትግራይ ጋር የተሳሰረ አይደለም።

በ ' ህወሓት ' የበላይነት ይመራ የነበረው የፌደራሉ መንግሥት ጥያቄያችንን ለማፈን በማኅበረሰቡ ተወካዮች ላይ እንግልት እና እስር ፈፅሟል።

ሐምሌ 05/2008 ዓ.ም. እኔ የምገኝበት የኮሚቴ አባላት አፍኖ ለመውሰድ የተደረገው ሙከራ ወደ ሕዝባዊ ተቃውሞ ተሸጋግሮ ነበር።

ባለፉት ጥቂት ዓመታት ውስጥ ሁኔታዎች በየጊዜው እየተቀያየሩ አሁን ላይ የማንነት አስመላሽ ኮሚቴ በአብላጫው የተሳተፈበት አስተዳደር ተመስርቶ አካባቢያችንን እያስተዳደርነው እንገኛለን።

የወልቃይት ሕዝብ የማንነት ጥያቄውን ለማስመለስ ጥረት ያደረገው ገና ህወሓት የትጥቅ ትግል በማካሄድ እያለ ጀምሮ ነው።

የአካባቢው ማኅበረሰብ ‘ከፋኝ’ በሚል አደረጃጀት የትጥቅ ትግል ሲያካሂድ ነበር።

ከመስከረም 2008 ዓ.ም ጀምሮ ደግሞ ከትግራይ ክልል እና ከፌደራል መንግሥቱ በሕገ መንግሥቱ መሠረት ምላሽ እንዲሰጠን ስንጠይቅ ነበር። "

ያንብቡ : https://telegra.ph/BBC-AMHARIC-06-19
በአቢሲኒያ ባንክ የከፍተኛ ትምህርት ቁጠባ የትምህርት ግቦችዎን ዛሬ ያሳኩ። የባንካችንን የትምህርት ልዩ የቁጠባ ሂሳብ ይጠቀሙ፣ከፍተኛ ወለድ ያግኙ።

#BankofAbyssinia #BankingService #BankinginEthiopia #SavingAccount #EducationSaving #HigherEducation #TheChoiceForAll #Ethiopia #የሁሉም_ምርጫ
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#EthioOnlineMarket

የተለያዩ ለኑሮ ጠቃሚ የሆኑ እቃዎችን ለማየት : https://publielectoral.lat/EOMMarket

የመረጡትን እቃ ይዘዙን፤ያሉበት ድረስ በነፃ  እናደርሳለን : 𝗣𝗵𝗼𝗻𝗲  ☞0929181818 / 0909868788

ይምጡ የሽያጭ ማእከሎቻችን ይጎብኙ፤ ተደስተው ይመለሳሉ !
አድራሻችን፦
• ቁጥር 1:- መገናኛ, ቤተልሄም ፕላዛ  የሱቅ
                 ቁጥር  G-10 ግራውንድ 
•ቁጥር 2:- ሜክሲኮ, ኬኬር ህንፃ የሱቅ  
                ቁጥር #338
•ቁጥር 3:- አያት አደባባይ , AAT CITY   
                  CENTER G-11 ግራውንድ
𝕵𝖔𝖎𝖓 𝖔𝖚𝖗 𝖈𝖍𝖆𝖓𝖓𝖊𝖑 @EOMmarket
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ቮልስዋገን

" ከቻይና ውጪ ያሉ ደንበኞች ለተሸከርካሪዎቹ የዋስትና መብት አያገኙም " - ቮልስ ዋገን

ባለፈው ሳምንት ID 4 እና ID 6 ክሩዝ የተባሉ የታዋቂው የጀርመን መኪና አምራች ቮልክስዋገን ስሪት የሆኑ የኤሌክትሪክ መኪኖች ወደ ኢትዮጵያ እንዳይገቡ እግድ መተላለፉ ይታወሳል።

ቅንጡዎቹ መኪኖች ለኢትዮጵያ ገበያ ላልተወሰነ ጊዜ እንዳይቀርቡ የታገዱት በመኪና አምራቹ ጥያቄ በኢትዮጵያ የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር አማካይነት ነው።

ጉዳዩን በተመለከተ #ቮልስዋገን ለቢቢሲ ማብራሪያ ሰጥቷል።

ምን አለ ?

" ወደ ኢትዮጵያ እንዳይገቡ እግድ እንዲያጣል የተደረገው በሁለት ዋነኛ ምክንያቶች ነው።

በቻይና የሚመረቱ የቮልክስዋገን ID.4፣ ID.6 X እና ID.6 CROZZ የተባሉት መኪኖች መቅረብ ያለባቸው #ለቻይና ገበያ ብቻ ነው ፤ መኪኖቹ ከቻይና ውጪ እንደማይሸጡ በሕግ ተደንግጓል።

ከዚህ በተጨማሪ ለቻይና ተብለው የተሰሩ ቮልክስዋገን ID መኪኖችን ከቻይና ውጪ ያሉ ደንበኞች የሚገዙ ከሆነ ለተሸከርካሪዎቹ የዋስትና መብት አያገኙም። " ብሏል።

ቮልስዋገን ፤ ሕጋዊ ፍቃድ የሌላቸው መኪና ሻጮች፣ መኪኖቹ ዓለም አቀፍ እውቅና እንዳላቸው በመግለጽ ለደንበኞቻቸው እየሸጡ እንደሆነ ደርሼበታለሁ ሲልም ገልጿል።

ነገር ግን ID 4፣ ID 6 X እና ID 6 ክሩዝ ለቻይና ብቻ ተብለው የተመረቱ በመሆናቸው መኪኖቹ ከቻይና ውጪ የሚያስፈልጋቸው ዋስትና የላቸውም ብሏል።

እነዚህ ከእውቅና ውጪ ወደ ኢትዮጵያ ገብተዋል የተባሉት መኪኖች በኢትዮጵያ " የቮልክስዋገን እውቅና ባላቸው ሻጮች ወይም ቮልክስዋገን ባጸደቃቸው ሰርቪስ ማድረጊያ ተቋማት ውስጥ ሁሉንም አይነት የመኪና ‘ሰርቪስ’ እና የጥገና አገልግሎት ሊያገኙ አይችሉም " ሲል አሳውቋል።

ፍቃድ የሌላቸው ሻጮች እነዚህን መኪኖችን ሕጋዊ እና ይፋዊ ባልሆነ መንገድ በተደጋጋሚ በሌሎች አገራት ለመሸጥ እየሞከሩ መሆኑን የገለፀው ቮልስዋገን ፤ ደንበኞች መኪኖችን ከመግዛታቸው በፊት ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ አሳስቧል።

ኩባንያው አገራት እነዚህን መኪኖች ወደ አገር ውስጥ እንዳያስገቡ ማሳሰቢያዎችን እያላከ መሆኑን ገልጾ፤ " ደንበኞች ID መኪኖችን ሲገዙ ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ እና ከሕጋዊ ወኪሎች ብቻ እንዲገዙ ያሳስባል " ብሏል።

የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር ምን አለ ?

(የሕዝብ ትራንስፖርት እና አሸከርካሪ ተሽከርካሪ መሪ ሥራ አስፈጻሚ የሆኑት አቶ ከድልማግስት ኢብራሂም)

" መኪኖቹን ያገድነው ለኢትዮጵያ መንገዶች ብቁ መሆናቸውን ማረጋገጥ ስለሚኖርብን ነው።

ተሸከርካሪዎቹ የደኅንነት ስጋት ሊሆኑ ይችላሉ ብለን አናስብም፣ ይሁን እንጂ በቅርብ ቀናት ከኤምባሲው ጋር ተነጋግረን ለሁሉም መልስ እንሰጣለን። "

መኪኖቹ በኢትዮጵያ ገበያ እንዲቀርቡ ሕጋዊ ፍቃድ ሳይኖራቸው እንዴት ከቻይና ሊመጡ ቻሉ ?

" የእግድ ጥያቄው ከኩባንያው የመጣው የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን ወደ አገር ውስጥ ማስገባት የሚቻልባቸው መመሪያዎች እና ደንቦች እየተዘጋጁ ባሉበት ወቅት ነው።

የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን ማስገቢያ ፍቃድ ገና በዝግጅት ላይ ነው።

ከዚህ በፊት ወደ አገር ውስጥ የገቡ የኤሌክትሪክ መኪኖች በነዳጅ የሚንቀሳቀሱ ተሸከርካሪዎች ሲሰተናገዱበት በነበረው መመሪያ ነው።

አሁን ላይ ወደ አገር ቤት ገብተው ለሽያጭ ያልቀረቡትን ቮልክስዋገን መኪኖችን በተመለከተ ለመነጋገር ከጀርመን ኤምባሲ ጋር በዚህ ሳምንት ቀጠሮ አለን። "

Via BBC AMHARIC

@tikvahethiopia
* አዲስ አበባ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፤ " ከጣሪያ እና ግድግዳ ግብር " ጋር በተያያዘ አንዳንድ አከራዮች በተከራዮች ላይ የዋጋ ጭማሪ እያደረጉ መሆኑን በክትትል ደርሼበታለሁ አለ።

የከተማ አስተዳደሩ ካቢኔ የካቲት 30 ቀን 2015 ዓ.ም  ባደረገው ውይይት ማንኛውም አከራይ የቤት ኪራይ እስከ ሰኔ 30 ቀን 2015 ዓ.ም ድረስ መጨመር የማይቻል መሆኑን መወሰኑ ያስታወሰው አስተዳደሩ፤ ማንኛውም አከራይ የቤት ኪራይ እስከ ሰኔ 30 /2015 ዓ.ም ድረስ መጨመርም ሆነ ተከራይ ማስወጣት የማይቻል መሆኑን አሳውቋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከአ/ አ ቤተሰቦቹ በደረሰው መልዕክት ከጣራ እና ግድግዳ ግብር ጋር በተያያዘ አከራዮች " ከፍተኛ ግብር ተጥሎብናል " በማለት በተከራዮቻቸው ላይ ከፍተኛ የኪራይ ጭማሪ በማድረግ ላይ ይገኛሉ።

ለአብነት አንድ የንግድ ተቋም ፤ የተጣለብኝን ከፍተኛ ግብር አሁን ባለው ኪራይ መሸፈን ስለማልችል ብሎ በተከራዮች ላይ  60% ጭማሪ እንደሚደረግ በመግለፅ ዝግጁ እንዲሆኑ አሳስቧል።

ሌሎች በተመሳሳይ " ከፍተኛ ግብር ተጣለብን " በማለት ተከራዮቻቸው ላይ የኪራይ ገንዝብ እየጨመሩ እንደሆነና ይህን የማያደርጉትንም እንደሚያስወጡ እየገለፁ እንደሚገኙ ከቲክቫህ ኢትዮጵያ አ/አ ቤተሰቦች ተጠቁሟል።

ውድ ቤተሰባችን እርሶስ ጭማሪ ተደርጎቦታል ? የከተማ አስተዳደሩ ያሳለፈው ኪራይ ያለ መጨመር እንዲሁም ተከራይን ያለማስወጣት ውሳኔ ተግባራዊነት ምን ያህል ነው ? @tikvah_eth_BOT

@tikvahethiopia
በዕለታዊ የዳታ ጥቅል ቅናሽ በ100% ስጦታ ታጅቦ ቀርቧል!

ከከፍተኛ ቅናሽ እና እጥፍ (100%) ስጦታ ጋር የቀረቡትን ዕለታዊ የዳታ ጥቅሎች ከሰፊው ገበታችን በቴሌብር ሱፐርአፕ እና ማይ ኢትዮቴል መተግበሪያዎች እንዲሁም በ*999# ይግዙ፤ ለሚወዷቸው በስጦታ ያበርክቱ!

ተጨማሪ ስጦታውን ከምሽቱ 4:00 እስከ ጠዋቱ 2:00 ሰዓት ፈታ ይሉበታል!

(ኢትዮ ቴሌኮም)
#Tigray

ትምህርት ሚኒስቴር ፤ በትግራይ ክልል በሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች ሲያስተምሩ ለነበሩ መምህራን ጥሪ ሊደረግ መሆኑን አሳውቋል።

በትግራይ ክልል በሚገኙ አራት ዩኒቨርሲቲዎች ሲያስተምሩ የነበሩ መምህራን የሰሜኑ ጦርነት መቀስቀስን ተከትሎ ተፈናቅለው በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች በጊዚያዊነት ተመድበው ሥራቸውን እንዲጀምሩ መደረጉ ይታወሳል።

"ነገር ግን አሁን ላይ ሁኔታዎች እየተስተካከሉ በመሆኑ መምህራኑ ወደቀድሞ ዩኒቨርሲቲዎቻቸው ተመልሰው ሥራቸውን እንዲቀጥሉ ጥሪ እንደሚደረግ" በትምህርት ሚኒስቴር የአስተዳደርና መሰረተ ልማት ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሰለሞን አብርሃ (ዶ/ር) ለኢፕድ ተናግረዋል፡፡

More : @tikvahuniversity
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#EthiopianAirlines

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአመታዊው የ " SKYTRAX " ውድድር ላይ በ5 ዘርፎች ሽልማት ተቀዳጀ።

አየር መንገዱ አሸናፊ የሆነባቸው ዘርፎች ፦

🇪🇹 " Best Airline in Africa 2023 " ለተከታታይ 6ኛ ግዜ፣

🇪🇹 " Best Business Class Airline in Africa 2023 " ለተከታታይ 5ኛ ግዜ፣

🇪🇹 " Best Economy Class Airline in Africa 2023 " ለተከታታይ 5ኛ ግዜ፣

🇪🇹 " Best Business Class Onboard Catering in Africa 2023 " ለተከታታይ 2ኛ ግዜ

🇪🇹 " Cleanest Airline in Africa 2023 " ዘርፎች ናቸው።

አየር መንገዱ ሽልማቶቹን በፈረንሳይ ፓሪስ በተዘጋጀው " Paris Air Show " መርሐ ግብር ላይ ተቀብሏል።

ምንጭ፦ የኢትዮጵያ አየር መንገድ

@tikvahethiopia