TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#AddisAbaba

የአዲስ አበባ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ዛሬ ባሰራጨው መልዕክት ፤ የከተማው ህዝበ ሙስሊም የነገን #ጁመአ በሰላም እንዲያሳልፍ ጥሪ አቅርቧል።

ምክር ቤቱ በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በሸገር ከተማ (ሲቲ) የመስጅድ ፈረሳ ጋር በተያያዘ ማህበረሰቡ ያቀረበውን ህገ መንግስታዊ የመብት ጥያቄዎች ማለትም የመስጅድ ፈረሳው ሙሉ በሙሉ እንዲቆም ፣ የፈረሱ መስጅዶችም ወደ ቀድሞው ቦታቸው እንዲመለስ መጅሊስ ዘጠኝ አባላት ያሉት ኮሚቴ በማቋቋም በጉዳዩ ዙሪያ በተለያዩ ደረጃዎች ከሚገኙ የመንግስት አካላት ጋር ውይይት እያደረገ ይገኛል ብሏል።

" መንግስትም የፍትህን መጓደል የጥያቄውን አሳሳቢነት፣ በሸገር ሲቲ አስተዳደር በውይይት ላይ ያልተመሰረተን አካሄድን ከግንዛቤ በማስገባት ለተከሰተው የመብት ጥሰት ፍትህ የማስፈን ሚናውን በአፋጣኝ እንደሚወጣ ተስፋ እናደርጋለን " ያለው ምክር ቤቱ ህዝቡ ኮሚቴው የደረሰበትን እስኪያሳውቅ ድረስ  ውጤቱን በትእግስትና በዱአ እንዲጠባበቅ  ጥሪ አቅርቧል።

የነገ የጁመአ ሰላት መላው የከተማው ሙስሊም በሁሉም መስጅዶች በሰላም ሰግዶ ወደ ቤቱ በሰላም እንዲመለስ ጥሪ የቀረበ ሲሆን በከተማው የሚገኙ ኢማሞች በሰላምና በትእግስት ዙሪያ የጁመአ ኹጥባ እንዲያደርጉ ማሳስቢያ ተላልፏል።

መንግስትም ጉዳዩን በፍጥነት እልባት እንዲሰጥ እና ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ በእስር ላይ የሚገኙ ዜጎችን ከእስር እንዲለቅ ምክር ቤቱ አጥብቆ ጠይቋል።

ባለፈው ሳምንት ጁመአ በሸገር ከተማ አስተዳደር ከሚደረገው የመስጂድ ፈረሳ ጋር በተያያዘ ምዕመናን የተቃውሞ ሰልፍ ማድረጋቸው ፤ የምዕመናን ህይወት ማለፉ ፣ ጉዳትም መድረሱ የሚዘነጋ አይደለም።

(ሙሉ መልዕክቱ ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
#አቢሲንያ_ባንክ

ባለውለታዎች !

ባንካችን ከ50 አመት በላይ ለሆናቸው ግለሰቦች ያዘጋጀው ልዩ የቁጠባ ሂሳብ ሲሆን ከመደበኛው የቁጠባ ሂሳብ ከፍ ያለ የወለድ መጠን የሚያስገኝ እና ከተለያዩ የአገልግሎት ክፍያዎች ላይ ቅናሽ የሚያገኙበት ነው፡፡ ለበለጠ መረጃ ድረ-ገፃችንን ይጎብኙ፡፡

https://www.bankofabyssinia.com/saving-account/

#BankofAbyssinia #BankingService #SeniorCitzens #WisdomAccount #Savings
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#MoE

አገር አቀፍ ፈተናዎች የሚሰጡባቸው እና የምረቃ ቀናት እንዲሁም የሬሜዲያ ፈተና ወጤት አያያዝ ላይ ቅያሪ ተደርጓል።

ትምህርት ሚኒስቴር ፤ ግንቦት 9 ቀን 2015 ዓ/ም ያስተላለፈውን ሴርኩላር በተመለከተ ከዩኒቨርሲቲዎችና ከክልል ት/ቢሮ አመራሮች ጋር በድጋሚ ግንቦት 22 ቀን 2015 በበይነ-መረብ ውይይት አድርጓል።

በውይይቱ መሰረትም ፦

- ፈተናዎች የሚሰጡባቸው ቀናት፣

- የተማሪዎች ምረቃ በዓል፣

- የሪሜዲያል ፈተና ውጤት አያያዝ በተመለከተ ቅያሪ መደረጉን ለሁሉም የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች፣ ለሁሉም የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት፣ ለሁሉም የክልል ትምህርት ቢሮዎች በፃፈው ደብዳቤ ገልጿል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ በኢፌዴሪ ትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ተፈርሞ የተላከውን ደብዳቤ #ትክክለኝነት ከሚመለከታቸው አካላት አረጋግጧል።

በዚህም ፦

- በ2014 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል አጠናቀው ፈተና በመውሰድ በልዩ ሁኔታ የሬሜዲያል ፕሮግራም ተጠቃሚ ለሆኑ ተማሪዎች ለአንድ ሴሚስተር የተሰጠው ትምህርት በማዕከል የጋራ ፈተና ተዘጋጅቶ ለተቋማት እንዲላክ ፤ ተቋማት ፊተናውን የማስተዳደር ውጤት የመግለፅና በ2016 ፍሬሽማን ፕሮግራም ለመከታተል ብቁ ሆነው የተገኙት (ማለትም በተቋማት የውስጥ ፈተና 30 ከመቶ፣ #በማዕከል የተዘጋጀው ፈተና 70 ከመቶ) ተደምሮ በድምሩ 50 ከመቶና ከዚያ በላይ ያስመዘገቡቱን እንዲያሳወቁ፣ ይህ አጠቃላይ ሂደት እስከ ሰኔ 30 ቀን ድረስ እንዲጠናቀቅ ትምህርት ሚኒስቴር አቅጣጫ አስቀምጧል።

- በ2015 ዓ/ም የመውጫ ፈተና ለመውሰድ የተመዘገቡ በግልና በመንግስት ተቋማት የሚገኙ እጩ ምሩቃንና ባለፉት ዓመታት የህግ መውጫ ፈተና ወስደው የማለፊያ ውጤት ያላስመዘገቡት ተማሪዎች የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች የመፈተኛ ማእከላት ውስጥ ፈተናው ከሐምሌ 3 እስከ 8 ባሉት ቀናት ተሰጥቶ ውጤት ሐምሌ 10 ቀን የሚገልጽ ይሆናል ተብሏል።

- የተማሪዎችን ምረቃ በተመለከተ ከሐምሌ 11 እስከ ሐምሌ 16 ቀን ባሉት ቀናት ውስጥ ማካሄድ የሚቻል መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር የገለፀ ሲሆን በመርሃ-ግብሩ ላይ የሚሳተፉት የመውጫ ፈተናውን ያለፉ ተማሪዎች #ብቻ ናቸው ብሏል።

- የ2015 የ12ኛ ከፍል ማጠቃለያ ፈተና ከሐምሌ 19 እስከ 30 የሚሰጥ ሆኖ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች ከሐምሌ 16 ቀን ጀምሮ ለዚሁ ሥራ ብቻ ዝግጁ እንዲሆኑ ትምህርት ሚኒስቴር አቅጣጫ አስቀምጧል።

(ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከሚመለከተው የትምህርት ሚኒስቴር አካል ትክክለኝነቱን ያረጋገጠው ደብዳቤ ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#AddisAbaba የአዲስ አበባ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ዛሬ ባሰራጨው መልዕክት ፤ የከተማው ህዝበ ሙስሊም የነገን #ጁመአ በሰላም እንዲያሳልፍ ጥሪ አቅርቧል። ምክር ቤቱ በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በሸገር ከተማ (ሲቲ) የመስጅድ ፈረሳ ጋር በተያያዘ ማህበረሰቡ ያቀረበውን ህገ መንግስታዊ የመብት ጥያቄዎች ማለትም የመስጅድ ፈረሳው ሙሉ በሙሉ እንዲቆም ፣ የፈረሱ መስጅዶችም ወደ…
#AddisAbaba

ዛሬ በአዲስ አበባ ፤ " አንዋር መስጂድ " ከጁመአ ስግደት መጠናቀቅ በኃላ የፀጥታ ኃይሎች በተከፈቱት ተኩስ የሰው ህይወት ስለማለፉና ጉዳት ስለመድረሱ በአካባቢው የሚገኙ የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት ጠቁመዋል።

በአሁን ሰዓት የተጎዱ ሰዎች እርዳታ እንዲያገኙ ጥሪ አቅርበዋል።

በመስጂዱ በነበረው ሁኔታ የአደጋ ጊዜ አዛን መሰማቱ ተነግሯል።

ከዚሁ ጋር በተያየ ኡስታዝ አቡበከር አህመድ ፤ " በታላቁ አንዋር መስጂድ የጁምዓ ሰላቱን ለመስገድ ከቤቱ የወጣን እና በመስጂድ ያለን ንፁሃን ህዝበ ሙስሊም ላይ ያለምንም ርህራሄ በጥይት የሀይል እርምጃ መውሰድ ኢ ሰብዓዊ ተግባር ነው " ብለዋል።

" ባዶ እጁን ለሰላት በወጡ ንፁሀን ላይ እየተወሰደ ያለውን የኃይል እርምጃ የፀጥታ ኃይሎች ያቆሙ ዘንድ አሳስባለሁ " ያሉቱ ኡስታዝ አቡበከር " በመስጂዱ ተጠልለው የሚገኙ እና ያለህራሄ በጥይት ተመትተው በመስጂዱ ውስጥ እና ዙሪያውን ወድቀው የሚገኙት ወንድሞቻችን በአስቸኳይ ወደ ህክምና ቦታ ይወሰዱ ዘንድ አምቡላንስ ወደ ቦታው እንዲገባ መንገዱን ክፍት ልታደርጉ ይገባል " ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል።

ስለ ዛሬው የአንዋር መስጂድ ሁኔታ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት እንዲሁም የአ/አ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት የሚሰጡት መረጃ / መግለጫ ካለ ተከታትለን እናሳውቃለን።

በተመሳሳይ በመንግስት / በከተማው አስተዳደር በኩል የሚሰጥ ማብራሪያ ካለ ተከታትለን የምናቀርብ ይሆናል።

ባለፈው ሳምንት ጁመአ በአንዋር መስጂድ በሸገር ከተማ እየተከናወነ ያለው የመስጂዶች ፈረሳ ተግባር በአፋጣኝ እንዲቆም ጥሪ በቀረበበት ወቅት በተወሰደ እርምጃ የሰዎች ህይወት ማለፉ የሚዘነጋ አይደለም።

ጥቆማ ፦ አምቡላንስ ለማግኘት 907 ወይም በ0115150608 ላይ ይደውሉ።

@tikvahethiopia
#EthioTelecom

የድምጽ ጥሪ ጥቅሎቻችን ከ100% ተመላሽ ጋር ቀረቡ!

ሁሉም የድምጽ ጥሪ ጥቅሎቻችን ከ100% ስጦታ ጋር እንዲሁም ወርሃዊዎቹ ተጨማሪ የኢንተርኔት ጥቅል ታክሎባቸው ይበልጥ ለእርስዎ ተስማሚ ሆነው ቀርበዋል

ከአይነተ ብዙ ሰፊ ልዩ የጥቅል ገበታችን በቴሌብር ሱፐርአፕ በድጋሚ ከ10% ስጦታ ጋር እንዲሁም በማይ ኢትዮቴል እና *999# ልብዎ የፈቀደውን ይዘዙ!
#ቴክኖ_ሞባይል

በቅርቡ ቴክኖ ሞባያል በኢትዮጵያ ያስተዋወቀው ዘመናዊ እና የተራቀቀው ፋንተም ቪ ፎልድ ስልክ ሞዴል !

የሚታጠፍ ወይም ፎልደብል የሞባይል ስልክ ቴክኖሎጂ በመያዝ የተመረተው ፋንተም ቪ ፎልድ ከልዩ ዲዛይኑ በተጨማሪ  ለተጠቃሚዎች ምቹ አገልግሎቶችን እንዲሰጥ ያስችለው ዘንድ ሲዘረጋ በባለ 7.85 ኢንች ሰፊ ስክሪን እንዲሁም ሲታጠፍ 6.42 ኢንች ስክሪን የያዘ ሲሆን በተጨማሪም በአገልግሎት ጊዜ በመተጣጠፉ ምክንያት እንከን እንዳይኖር የሚያረገው የኤሮስፔስ ግሬድ ሂንጅ ተገጥሞለታል። 

የፋንተም ቪ ፎልድ በባለ 5 ሌንስ ሲስተም የሚተገብር ካሜራ በመጠቀም እጅግ ከፍተኛ ጥራት (ultra-HD) ያላቸው ምስሎችን የማንሳት አቅም አለው።

ዘመኑ ያፈራውና ከፍተና አቅም እንዳለው የሚነገርለትን ሚዲያቴክ ዲምነሲቲ 9000 የተባለ ፕሮሰሰር ከ256 ጂቢ ሜሞሪ እና 12ጂቢ ራም የያዘው ፋንተም ቪ ፎልድ ማንኛውንም አይነት መተግበሪያ በፍጥነት እና ያለእንከን እንዲሰራ የማስቻሉ ልዩ አቅም ብሎም በሞባይል ስልክ በመጠቀም ብዙ ስራዎችን ለሚሰሩ ባለሙያዎች እና ሀላፊዎቸ ተመራጭ ያደርገዋል።
TIKVAH-ETHIOPIA
#AddisAbaba ዛሬ በአዲስ አበባ ፤ " አንዋር መስጂድ " ከጁመአ ስግደት መጠናቀቅ በኃላ የፀጥታ ኃይሎች በተከፈቱት ተኩስ የሰው ህይወት ስለማለፉና ጉዳት ስለመድረሱ በአካባቢው የሚገኙ የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት ጠቁመዋል። በአሁን ሰዓት የተጎዱ ሰዎች እርዳታ እንዲያገኙ ጥሪ አቅርበዋል። በመስጂዱ በነበረው ሁኔታ የአደጋ ጊዜ አዛን መሰማቱ ተነግሯል። ከዚሁ ጋር በተያየ ኡስታዝ አቡበከር አህመድ…
" የፀጥታ ኃይሎች ቀውሱን ከሚያባብሱ እርምጃዎች ሊቆጠቡ ይገባል " - ኡስታዝ አቡበከር አህመድ

ኡስታዝ አቡበክር አህመድ ፤ ዛሬ ከጁሙዓ በኋላ በንፁሃን ሰጋጆች ላይ በተወሰደው የኃይል እርምጃ በርካታ ሙስሊሞች ላይ ጉዳት መድረሱን ገለፁ።

ከአንድ ሰዓት በፊት ባሰራጩት መልዕክታቸው ፤ የህክምና እርዳታ ማግኘት ያልቻሉ ብዙ መሆናቸውንና ይህንን ቀውስ ለመፍታት በአስቸኳይ አምቡላንስ መግባት እንዳለበት አሳስበዋል።

" የፀጥታ ኃይሎች ቀውሱን ከሚያባብሱ እርምጃዎች በመቆጠብ ወደቦታው የመጅሊስ አመራሮች እና የሙስሊሙ የማህበረሰብ መሪዎች እንዲገቡና መረጋጋት እንዲፈጥሩ ሊፈቅዱ ይገባል " ብለዋል።

በጥይት ተመትተው ደማቸው እየፈሰሱ ያሉ ሙስሊሞች እርዳታ ሊያገኙ ይገባል ሲሉ አስገንዝበዋል።

በሌላ በኩል ፤ ለጁምዓ ሰላት ወደ አንዋር መስጂድ ገብተው ከመስጂድ ውስጥ እንዳይወጡ መንገድ የተዘጋባቸው ምዕመናን እስካሁን መውጣት እንዳልቻሉ ተነግሯል።

የተለያዩ ተፅዕኖ ፈጣሪ ሙስሊም ምሁራን  በአካባቢው ተገኝተው የማረጋጋት ስራና በመስጂድ ውስጥ ያሉትን ምዕመናን ለማስለቀቅ ሙከራ እያደረጉ መሆኑን ዛውያ ቴሌቪዥን ዘግቧል።

በአንዋር መስጂድ ውስጥ የሚገኙ ምዕመናን የአስር ሰላታቸውን በሰላተል ኸውፍ ዲናዊ ስርአት ሰግደው በመስጂድ ውስጥ ተቀምጠው ይገኛሉ ተብሏል።

ሰዓቱ እየመሸ ስለሆነ መጅሊስ እና የሚመለከተው አካል ሁሉ የበኩሉን እንዲወጣና መንገዱ ተከፍቶ እንዲወጡ እንዲደረግ ጥሪ ቀርቧል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#AddisAbaba ዛሬ በአዲስ አበባ ፤ " አንዋር መስጂድ " ከጁመአ ስግደት መጠናቀቅ በኃላ የፀጥታ ኃይሎች በተከፈቱት ተኩስ የሰው ህይወት ስለማለፉና ጉዳት ስለመድረሱ በአካባቢው የሚገኙ የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት ጠቁመዋል። በአሁን ሰዓት የተጎዱ ሰዎች እርዳታ እንዲያገኙ ጥሪ አቅርበዋል። በመስጂዱ በነበረው ሁኔታ የአደጋ ጊዜ አዛን መሰማቱ ተነግሯል። ከዚሁ ጋር በተያየ ኡስታዝ አቡበከር አህመድ…
#Update

ኡስታዝ ሐሰን ታጁ (አምባሳደር) ፤ " የኃይል እርምጃ በየትኛዉም መመዘኛ ተቀባይነት የለዉም " አሉ።

ኡስታዝ ሐሰን " በዛሬዉ ዕለት በታላቁ አንዋር መስጂድና በሌሎች መስጂዶች የመንግስት የጸጥታ ሀይሎች የወሰዱት የንጹሀን ዜጎችን ህይወት የቀጠፈና ያቆሰለ የሀይል እርምጃ በየትኛዉም መመዘኛ ተቀባይነት የለዉም " ብለዋል።

" እንዲህ ዓይነት ያልተገቡ እርምጃዎች ቀዉስን በማባባስና የማህበረሰቡን ምሬት በመጨመር በሀገር ላይ አደጋ የሚደቅኑ አላስፈላጊ ዉጤቶችን ሊያስከትሉ እንደሚችሉ የሚመለከተው አካል ሊረዳ በተገባ ነበር፡፡ " ሲሉ ገልጸዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#እንድታውቁት የኣክሱም ዩኒቨርሲቲ በጦርነት ምክንያት ተቋርጦ የቆየውን የመማር ማስተማር ሂደት ለማስቀጠል በዝግጅት ላይ እንደሆነ ገልጿል። በመሆኑም በሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች ትምህርታቸውን እየተከታተሉ #የማይገኙ ሁሉም የዲግሪ (መደበኛ፣ ኤክስቴንሽን፣ ክረምት) እንዲሁም የማስተርስ (መደበኛ፣ ኤክስቴንሽን ፣ ክረምት) ተማሪዎች ከዚህ በታች ባለው ሊንክ እንዲመዘገቡ ጥሪ ቀርቧል። ሊንክ ፦ http://196.190.28.50…
#Update

ራያ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በአካል ቀርበው እንዲመዘገቡ ጥሪ አቀረበ።

ራያ ዩኒቨርሲቲ በመደበኛና ተከታታይ ትምህርት መርሐ ግብር ትምህርታቸውን ለመከታተል ቀደም ሲል ዩኒቨርሲቲዉ ባወጣዉ ማስታወቅያ መሰረት የተመዘገቡ (የዩኒቨርሲቲዉና ከሌሎች ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ያመለከቱ) ተማሪዎች ሰኔ 6 እና 7 / 2015 ዓ.ም በራያ ዩኒቨርሲቲ ሬጅስትራርና አልሙናይ ዳይሬክቶሬት በአካል በመገኘት እንዲመዘገቡ ጥሪ አቅርቧል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" የፀጥታ ኃይሎች ቀውሱን ከሚያባብሱ እርምጃዎች ሊቆጠቡ ይገባል " - ኡስታዝ አቡበከር አህመድ ኡስታዝ አቡበክር አህመድ ፤ ዛሬ ከጁሙዓ በኋላ በንፁሃን ሰጋጆች ላይ በተወሰደው የኃይል እርምጃ በርካታ ሙስሊሞች ላይ ጉዳት መድረሱን ገለፁ። ከአንድ ሰዓት በፊት ባሰራጩት መልዕክታቸው ፤ የህክምና እርዳታ ማግኘት ያልቻሉ ብዙ መሆናቸውንና ይህንን ቀውስ ለመፍታት በአስቸኳይ አምቡላንስ መግባት እንዳለበት አሳስበዋል።…
ሸይኽ ሱልጣን አማን ኤባ አንዋር መስጂድ ይገኛሉ።

የአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ም/ቤት ፕሬዝዳንት ሸይኽ ሱልጣን አማን ኤባ በአሁን ሰአት አንዋር መስጂድ እንደሚገኙ ተገልጿል።

ሸይኽ ሱልጣን አማን ኤባ ከሚመለከተው አካል ጋር በመነጋገር በሰዎች ላይ የሚደርሱ ችግሮች እንዳይባባሱ እና በመስጂዱ ጊቢ ውስጥ የሚገኙትን ሰዎች በሰላም ወደ ቤታቸው እንዲሄዱ ለማድረግ ጥረት እያደረጉ ይገኛሉ ሲል ከፍተኛ ምክር ቤቱ አሳውቋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ሸይኽ ሱልጣን አማን ኤባ አንዋር መስጂድ ይገኛሉ። የአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ም/ቤት ፕሬዝዳንት ሸይኽ ሱልጣን አማን ኤባ በአሁን ሰአት አንዋር መስጂድ እንደሚገኙ ተገልጿል። ሸይኽ ሱልጣን አማን ኤባ ከሚመለከተው አካል ጋር በመነጋገር በሰዎች ላይ የሚደርሱ ችግሮች እንዳይባባሱ እና በመስጂዱ ጊቢ ውስጥ የሚገኙትን ሰዎች በሰላም ወደ ቤታቸው እንዲሄዱ ለማድረግ ጥረት እያደረጉ ይገኛሉ ሲል ከፍተኛ…
#Update

በታላቁ አንዋር መስጂድ በሰላማዊ ምእመናን ላይ የደረሰውን ጉዳት ተከትሎ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ሼይኽ ሐጂ ኢብራሒም ቱፋ ከሚመለከተው የፌደራል ፓሊስ ኮሚሽን ጋር የተፈጠረውን ቀውስ ለማረጋጋት እና ባስቸኳይ የተጎዱትን ለማትረፍ በሚቻልበት መንገድ ላይ እየተነጋገሩ መቆየታቸው ተሰምቷል።

በተፈፀመው ጥቃት ጉዳት የደረሰባቸው ምዕመናን የህክምና እርዳታ እንዲያገኙ ወደ ሆስፒታል እንዲወሰዱ አምቡላስ ወደ ቦታው እንዲደርስ እያደረጉ ይገኛሉም ተብሏል።

ታላቁ አንዋር መስጂድ ከውጥረት ነፃ እንዲሆን ፣በመስጂዱ ውስጥ የሚገኙ ምዕመናንም በሰላም ወደቤታቸው እንዲገቡ የአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ፕሬዝደንት ሼይኽ ሱልጣን አማንን ጨምሮ ሶስት ከፍተኛ አመራሮች ከመጅሊሱ ተወክለው ወደ ቦታው በማምራት ከፀጥታ ኃይሉ ጋር ይህን ተፈፃሚ እንዲሆን እየሰሩ ይገኛሉ ተብሏል።

ከሁሉም ነገር በፊት #ሰብኣዊነት መቅደም ስለሚኖርበት የተጎዱትን ወደ ህክምና ቦታ ለማድረስ እና በመስጂዱ ያሉ ምዕመናን በሰላም ወደቤታቸው እንዲገቡ ለማድረግ በሚደረገው ጥረት በአንዋር መስጂድ እና በዙርያው ያለው የፀጥታ ኀይልም ይህ ተፈፃሚ እንዲሆን የበኩሉን ሓላፊነት እንዲወጣ ጥሪ ቀርቧል።

(ኡስታዝ አቡበከር አህመድ)

@tikvahethiopia