TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#AddisAbaba

በተለምዶ ሰይጣን ቤት ወይም ፒራሚድ አዲስ እና ባስ አዲስ ክለብ ታሸጉ ፤ 68 ሰዎችም በቁጥጥር ስር ውለዋል።

በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 3 አስነዋሪ ድርጊት እና ትውልድን በሚጎዳ ስራ ላይ የተሰማሩና ሲጠቀሙ የተገኙ 68 ሰዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የከተማው አስተዳደር አሳውቋል።

ከህብረተሰቡ በደረሰ ጥቆማ በተደረገ #ድንገተኛ_ፍተሻ በተለምዶ #ሰይጣን_ቤት ወይም #ፒራሚድ_አዲስ እና #ባስ_አዲስ_ክለብ በማህበረሰቡ ተቀባይነት የሌላቸው አፀያፊ ድርጊቶች ሌሎች ህገወጥ ተግባራት ሲፈፅሙ በመገኘታቸው ቤቶቹ መታቸጋቸው ተገልጿል።

የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር፣ የአዲስ አበባ ከተማ ፖሊስ እና የሠላምና ፀጥታ ቢሮ በጋራ በመሆን ትላንት ከምሽቱ 4:00 ሰዓት እስከ 8:00 ሰዓት ባደረጉት ድንገተኛ ፍተሻ ነው ህገወጥ ተግባራት ሲፈጸምባቸው የተገኙት የምሽት ቤቶች እንዲታሸጉ የተደረገው።

በተደረገው ድንገተኛ ፍተሻ ፦

- ከ100 በላይ የሺሻ ዕቃዎች ፣
- በርካታ መዋሰሎች፣
- ከ6 በላይ ሀሺሽ የያዙ እቃዎች እንዲሁም በወቅቱ በቦታው የነበሩ ከ68 በላይ የሚሆኑ ተጠቃሚዎችን እና ወጣቱን በዚህ እኩይ ድርጊት ላይ እንዲሳተፍ ሲያደርጉ የቆዩ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የከተማው አስተዳደር ገልጿል።

ነዋሪዎች በየአከባቢያቸው አዋኪና ከማህበረሰቡ ወግና ባሕል ያፈነገጡ አስነዋሪ ድርጊቶች ላይ ወጣቱ እንዲሳተፍ የሚያደርጉ ምሽት ቤቶችንና ግለሰቦችን በማጋለጥ ሀላፊነቱን እንዲወጣ ጥሪ ቀርቧል።

#MayorOfficeofAddisAbaba

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#TPLF የኢፌዴሪ ሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት በአሸባሪነት የሰየመውን ሕዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ሕወሓት) የሽብርተኝነት ስያሜ #ይነሳ #አይነሳ በሚለው ጉዳይ ላይ ዛሬ ውሳኔ ያሳልፋል ተብሎ እንደሚጠበቅ ሪፖርተር ጋዜጣ ዘግቧል። በምክር ቤቱ ውስጥ የብልፅና አባላት ሕወሓትን ከአሸባሪነት ለመሰረዝ ያለመ ዝግ ስብሰባ ትናንት መጋቢት 12 ቀን 2015 ዓ.ም. የምክር ቤቱ አፈ ጉባዔን ጨምሮ፣ የፍትህ ሚኒስትሩ…
#Update

ህወሓት ከሽብርተኛ ድርጅትነት #ተሰረዘ

የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሕዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ከሽብርተኛ ድርጅት እንዲሠረዝ ውሳኔ አሳለፈ፡፡

ምክር ቤቱ ዛሬ ባሄደው ልዩ ስብሰባ ህወሓትን ከሽብርተኛ መዝገብ ለማንሳት በቀረበለት የውሳኔ ሀሳብ ላይ ከተወያየ በኋላ በአብላጫ ድምፅ ውሳኔውን አፅድቋል።

#ኤፍቢሲ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update ህወሓት ከሽብርተኛ ድርጅትነት #ተሰረዘ። የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሕዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ከሽብርተኛ ድርጅት እንዲሠረዝ ውሳኔ አሳለፈ፡፡ ምክር ቤቱ ዛሬ ባሄደው ልዩ ስብሰባ ህወሓትን ከሽብርተኛ መዝገብ ለማንሳት በቀረበለት የውሳኔ ሀሳብ ላይ ከተወያየ በኋላ በአብላጫ ድምፅ ውሳኔውን አፅድቋል። #ኤፍቢሲ @tikvahethiopia
#TPLF

" ሽብርተኝነቱን ማንሳቱ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም ይረዳል " - ዶ/ር ጌዲዮን ጢሞቲዮስ

ህወሓት ከሽብርተኛ ድርጅትነት በአብላጫ ድምፅ ተሰርዟል።

የፍትህ ሚኒስትሩ ዶክተር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ በዛሬው የምክር ቤት ልዩ ስብሰባ ወቅት ፤ " የሰላም ስምምነቱ ቀሪ ጉዳዮች ቢኖሩም ሽብርተኝነቱን ማንሳቱ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም ይረዳል " ሲሉ መናገራቸውን የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ዘግቧል።

ምክር ቤቱ ህወሓትን ከሽብርተኛ ድርጅት ዝርዝር ያነሳው የፕሪቶሪያውን ስምምነት ተከትሎ ነው።

በስምምነቱ አንቀጽ 7/2 C መሰረት የፌዴራል መንግሥት በህወሓት / TPLF / ላይ የተጣለውን የሽብርተኝነት ስያሜ በምክር ቤቱ እንዲነሳ ሁኔታዎችን እንደሚያመቻች ይገልጻል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#TPLF " ሽብርተኝነቱን ማንሳቱ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም ይረዳል " - ዶ/ር ጌዲዮን ጢሞቲዮስ ህወሓት ከሽብርተኛ ድርጅትነት በአብላጫ ድምፅ ተሰርዟል። የፍትህ ሚኒስትሩ ዶክተር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ በዛሬው የምክር ቤት ልዩ ስብሰባ ወቅት ፤ " የሰላም ስምምነቱ ቀሪ ጉዳዮች ቢኖሩም ሽብርተኝነቱን ማንሳቱ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም ይረዳል " ሲሉ መናገራቸውን የኢትዮጵያ ፕሬስ…
#TPLF

ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ / ህወሓት / ከሽብርተኛ ድርጅትነት በተሰረዘበት የዛሬው የኢፌዴሪ ህዝብ ተወካዮች ም/ቤት ልዩ ስብሰባ ላይ 280 የፓርላማ አባላት ተገኝተው ነበር።

ከተገኙት የፓርላማ አባላት መካከል 61 የፓርላማ አባላት ህወሓት ከሽብርተኛ ድርጅትነት መሰረዙን #ተቃውመው ድምፅ ሰጥተዋል።

5 የፓርላማ አባላት ድምፀ ተአቅቦ አድርገዋል።

በዚህም #በአብላጫ_ድምፅ ህወሓት ከሽብርተኛ ድርጅትነት ይነሳ የሚለው የውሳኔ ሃሳብ ፀድቋል።

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ውሳኔውን ተከትሎ ባሰራጨው መረጃ ፤ " በህወሓትና በፌደራል መንግስት በኘሪቶሪያ የተደረገውን ሥምምነት ለማጽናት ህወሐትን ከሽብርተኝነት ስያሜ ማንሳት #አማራጭ_የሌለው ጉዳይ መሆኑን የውሳኔ ሃሳቡ በቀረበበት ወቅት ተነስቷል " ብሏል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update

የብፁዕ አቡነ አረጋዊ (ዶ/ር) እና የብፁዕ አቡነ ባስልዮስ ሥርዓተ ቀብር እሑድ መጋቢት 17 ቀን 2015 ዓ.ም በመንበረ ጸባኦት ቅደስት ሥላሴ ካተድራል እንደሚፈጸም የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ (ዶ/ር) መግለፃቸውን የኢኦተቤ ቴሌቪዥን ዘግቧል።

ብፁዕ አቡነ አረጋዊ (ዶ/ር) ለረጅም ጊዜ በሀገር ውስጥ እና በውጭ በህክምና ሲረዱ ቆይተው ሊሻላቸው ሳይችል ቀርቶ ትላንት ከዚህ ዓለም በሞተ ስጋ መለየታቸው መገለፁ ይታወቃል።

ብፁዕ አቡነ ባስልዮስ ሣልሳይ መጋቢት 01 ቀን 2015 ዓ/ም ምሽት ነበር ከዚህ ዓለም ድካም ያረፉት።

ብፁዕ አቡነ ባስልዮስ ሣልሳይ ከ፲፯ ዓመታት በፊት በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ፓትርያርክ ርእረ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ አንብሮተ ዕድ የተሾሙ ነበሩ።

ብፁዕነታቸው አስኬማ መላእክት ከሚለበስበት የኤጲስ ቆጶስነት ሹመት በፊት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ኢትዮጵያ ውስጥ በተለያዩ አካባቢዎች ሲያገለግሉ እንደነበር ታሪካቸው ያስረዳል።

ብፁዕነታቸው በሰሜን አሜሪካ በኒውዮርክ ሀገረ ስብከት በሚገኘው በመንበረ ጵጵስና ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን ከአገልጋይነት እስከ የበላይ ጠባቂነት በአባትነት አገልግለዋል።

ብፁዕ አቡነ ባስልዮስ ሣልሳይ የኒውዮርክ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስም ነበሩ።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
ፎቶ፦ በዓለም አቀፍ ደረጃ እጅግ የሚከበሩት እና የሚታወቁት የአካባቢ ጉዳይ ሳይንቲስት ዶክተር ተወልደብርሃን ገብረ እግዚአብሔር የቀብር ስነ ስርዓት ዛሬ ተፈፅሟል።

ስርዓተ ቀብራቸው በአዲስ አበባ በመንበረ ጸባኦት ቅድስት ስላሴ ካቴድራል ነው የተፈፀመው።

ዶ/ር ተወልደብርሃን ገ/እግዚአብሔር ባደረባቸው ሕመም በሕክምና ሲረዱ ቆይተው ትናንት መጋቢት 12 ቀን 2015 ዓ/ም ሕይወታቸው ማለፉ ይታወቃል።

#ENA

@tikvahethiopia