TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
" የተዘረፍነው ካሜራን ጨምሮ ሙሉ ንብረቶቻችንን ነው " - ጋዜጠኛ ሙልጌታ አንበርብር ከኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን ህጋዊ ፍቃድ አግኝቶ በኦንላይ ሚዲያ እየተንቀሳቀሰ የሚገኘው " ኢትዮ 251 " ሚዲያ ካሜራን ጨምሮ ሙሉ ንብረቶቹን እንደተዘረፈ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አሳውቋል። ሚዲያው ዘረፋው የተፈጸመው ትናንት ዕሁድ መጋቢት 10/2015 ዓ/ም መሆኑን ገልጿል። የኢትዮ 251 ሚዲያ ባለቤትና…
ሌላ ዝርፊያ ...

" ከድርጅታችን 250 ሺህ ብር የሚገመት ንብረት ተዘርፏል " - ጋዜጠኛ ሚኪያስ ጌታቸው

ከኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን ህጋዊ ፍቃድ አግኝቶ በኦንላይን የሚንቀሳቀሰው " ዩሪካ ቲቪና ሬድዮ " ከቢሮው 250 ሺህ ብር የሚገመት ንብረት እንደተዘረፈ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አሳውቋል።

ድርጅቱ ዝርፊያው የተፈፀመበት አራት ኪሎ ከሚገኘው " ተስኒም ህንፃ " 5ኛ ፎቅ መሆኑን አመልክቷል።

ዩሪካ ቲቪና ሬድዮ ባለቤት እና ስራ አስኪያጅ ጋዜጠኛ ሚኪያስ ጌታቸው  " ሁለት Canon Camera Body ፣  ሶስት Canon Camera Lens እና አንድ laptop አሁን ባለው የገበያ ዋጋ አጠቃላይ ግምታቸው 250ሺህ ብር የሚደርስ ንብረት አራት ኪሎ ከሚገኘው ተስኒም ህንፃ 5ኛ ስቱዲዮችን ተዘረፏል " ብሏል።

ዘረፋው እንደ ተፈጸመው የታወቀው ትናንት ዕሁድ መጋቢት 10 ቀን 2015 ዓ.ም ከቀኑ ከቀኑ 7:20 ሰዓት ላይ እንደነበር ገልጾልናል።

" አርብ መጋቢት 8 የዕለቱን ስራችን አጠናቀን ከቢሮ ወጣን። በንጋታው ቅዳሜ ስለሆነ ስራም ስላልነበረን ቢሮ አልገባንም። ከአርብ 11:00 ጀምሮ እስከ እሁድ 7:00 ድረስ እኔም ሆንኩ ባልደረቦቼ ቢሮ አልገባንም። እሁድ ዕለት ግን ለሰኞ ማስረከብ ያለበትን ስራ ለማጠናቀቅ አንደኛው የኤዲቲንግ ባለሙያ ቢሮ በገባበት ወቅት ነው ዝርፊያ መፈፀሙን ያወቅነው " ሲል ሁኔታውን አስረድቷል።

ጋዜጠኛ ሚኪያስ ጌታቸው በነገው ዕለት በራሱ " ዩሪካ ቲቪና ሬድዮ " የዩትዩብ ገፅ ላይ ማብራሪያ እንደሚሰጥ ገልጿል።

በዛው 4 ኪሎ አካባቢ ከኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን ህጋዊ ፍቃድ አግኝቶ በኦንላይ ሚዲያ እየተንቀሳቀሰ የሚገኘው " ኢትዮ 251 " ሚዲያ ካሜራን ጨምሮ ሙሉ ንብረቶቹን (ከ1.7 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት) እንደተዘረፈ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ማሳወቁ ይታወሳል።

@tikvahethiopia
#አቢሲንያ_ባንክ

በካሽ ጎ ገንዘብ ወደ ሀገር ቤት ሲልኩ ምንም ሳይሸራረፍ እንደ አደራ እቃ በአስተማማኝነት እና በፍጥነት ይደርሳል።

ቪዛ ወይም ማስተር ካርድዎን ተጠቅመው በካሽጎ ገንዘብ ወደ ኢትዮጵያ ማስተላለፍ ይችላሉ፡፡

ነፃ፣ ምቹ እና ቀላል፡፡ የሞባይል መተግበሪያውን ከ Play Store ወይም App Store በማውረድ ይጠቀሙ።

ለአንድሮይድ ስልኮች 👇
https://play.google.com/store/apps/details?id=com.bankofabyssinia.cashgo&hl=en&gl=US

ለአፕል ስልኮች 👇
https://apps.apple.com/us/app/cashgo/id1559346306
#CashGo #visa #mastercard #የሁሉም_ምርጫ
#ዶክተር_ተወልደብርሃን_ገብረእግዚአብሔር

የአካባቢ ጉዳይ ተመራማሪ ዶ/ር ተወልደ ብርሃን ገብረ እግዚአብሔር በ83 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል።

ዶክተር ተወልደ ብርሃን ገብረ እግዚአብሔር  ማን ነበሩ ?

- ከአባታቸው ቄስ ገብረ እግዚአብሔር ዮሐንስ እና ከእናታቸው ወ/ሮ መዓዛ ወልደመድህን በትግራይ ክልል፣ ዓድዋ  ርባገረድ መንደር በ1932 ዓ/ም ነው የተወለዱት።

- የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርታቸውን በንግስተ ሳባ 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እና የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በዊንጌት ተምረዋል፤ 1959 ከፍተኛ ውጤት አምጥተው ወደ ቀዳማይ ኃላይለስላሴ ዩኒቨርሲቲ  / በኃላ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ገብተው ትምህርታቸውን ተከታትለዋል።

- በአካባቢ ጉዳይ ላይ ለዓለም የሚጠቅም ተጠቃሽ ሥራዎችን ሰርተዋል።

- በብዝሐ ሕይወት ፣ በማሕበረሰብ (የአርሶ አደሮችን መብት) ማስከበር እና በዘረመል ምሕንድስና በሚመረት እህል ላይ ያደረጓቸው ምርምሮች በዓለም አቀፍ ደረጃ ዕውቅናና ሽልማት አስገኝቶላቸዋል።

- ካገኟቸው ከዓለም አቀፍ ሽልማታቸው መካከል " የአማራጭ የኖቤል ሽልማት " እና " የምድራችን ጀግና " በሚል ሲንጋፖር ላይ በፈረንጆቹ 2006 ላይ የተሸለሙት ይጠቀሳሉ።

- ሕይወታቸው እስከአለፈበት ድረስም አዲስ አበባ ይኖሩ እንደነበር።

- ዶ/ር ተወልደብርሃን በተወለዱ በ83 ዓመታቸው ባደረባቸው ህመም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል።

- ዶክተር ተወልደ ብርሃን የሦስት ሴቶች ልጆች አባት ነበሩ፡፡ እንዲሁም ከ60 በላይ ሌሎች ልጆችን አሳድገዋል፡፡

Credit : #ኤፍቢሲ #ኤኤምሲ

@tikvahethiopia
" ሁሉም ተፋላሚ ወገኖች የጦር ወንጀሎችን ፈፅመዋል " - አንቶኒ ብሊንከን

አሜሪካ በትግራይ ተቀስቅሶ ወደ አማራ እና አፋር ክልሎች በተዛመተው ጦርነት ሁሉም ተፋላሚ ወገኖች የጦር ወንጀሎች ፈጽመዋል የሚል ድምዳሜ ላይ መድረሷን አሳውቃለች።

ይህንን ያሳወቀችው ትላንት በውጭ ጉዳይ ቢሮዳ በኩል የአገራትን የሰብዓዊ መብቶች ይዞታን በተመለከተ የሚያደርገው ግምገማ ዓመታዊ ሪፖርት ይፋ ስታደርግ ነው።

ሪፖርቱን ይፋ ያደረጉት በቅርቡ አዲስ አበባ መጥተው ከፌዴራል እና ከህወሓት አመራሮች ጋር መክረው የተመለሱት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ አንቶኒ ብሊንከን ናቸው።

ብሊንከን ምድነው ያሉት ?

- የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት፣ የኤርትራ ጦር፣ የህወሓት ኃይሎች እና የአማራ ኃይሎች የጦር ወንጀሎች ፈጽመዋል።

- ከጦር ወንጀሎች በተጨማሪ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት፣ የኤርትራ ጦር እና የአማራ ኃይሎች ግድያዎችን፣ መድፈር እና አስገዳጅ ስደትን ጨምሮ በሰብዓዊነት ላይ የሚፈጸም ወንጀል ፈጽመዋል።

- የአማራ ኃይሎች አባላት በምዕራብ ትግራይ አስገዳጅ ማፈናቀል እና የዘር ማጽዳት ወንጀል ፈፅመዋል። 

- እነዚህ ወንጀሎች ብዙዎቹ በዘፈቀደ ወይም በጦርነት ውስጥ የተከሰቱ ሳይሆን ሆን ተብለው ታስበው የተፈጸሙ ናቸው።

- ይህን ድምዳሜ ያስተለለፍነው መረጃዎችን መርምረን ነው፤ ይህ ድምዳሜ በአሜሪካ ፖሊሲ ላይ ወዲያውኑ የሚያስከትለው ለውጥ አይኖርም። ወንጀሎቹን የፈጸሙ አካላት ግን ተጠያቂ ሊሆኑ ይገባል።

- ሁሉም ወገኖች ለፈጸሙት ግፍ እውቅና መስጠት ዘላቂ ሰላም ለማምጣት ወሳኝ እርምጃ ነው። በኃላፊነት ቦታ ላይ የተቀመጡትን ጨምሮ ጥሰቶቹን የፈጸሙ አካላት ተጠያቂ ሊሆኑ ይገባል።

ብሊንከን ከሰሞኑን በነበራቸው የኢትዮጵያ ቆይታ ወቅት ከፌዴራል እና ከህወሓት ባለስልጣናት ጋር መነጋገራቸውን ገልጸዋል።

ይህንን በተመለከተ እንዲህ ብለዋል ፦

" ሁለቱም ወገኖች ግጭትን በዘላቂነት ለመፍታት በደረሱት ስምምነት ላይ እና በአተገባበሩ ላይ ስለደረሱበት ጉልህ መሻሻል አመስግነናቸዋል።

ስምምነቱን ተከትሎ ጦርነቱ ቆሟል፤ ሰብዓዊ እርዳታን እየገባ ነው ፣ መሠረታዊ አገልግሎቶችም እየተመለሱ ነው፤ የኤርትራ ኃይሎች እየወጡ ናቸው።

ሆኖም ዘላቂ ሰላምን ለመገንባት ሁሉም ወገኖች ለፈጸሟቸው ግፎች እውቅና መስጠት አለባቸው ከዕርቅ ጋር ተጠያቂነት ሊመጣ ይገባል፤ ይህን ከባለስልጣኖች ጋር ተነጋግሬያለሁ።

ተፋላሚ ወገኖች ለተፈጸሙ ጥሰቶች ተጠያቂነት ለማስፈን የገቡትን ቁርጠኝነትም በበጎ የምንመለከተው ነው።

ከዚህም ጋር ተያይዞ የኢትዮጵያ መንግሥት መጠነ ሰፊ ጥሰት ከተፈጸመባቸው አገራት ተሞክሮን በማጎልበት የሸግግር ፍትህ አማራጭን በማምጣት የመጀመሪያ እርምጃ ወስዷል።

የሽግግር ፍትህ ሁሉን አካታች፣ ተዓማኒ እና በተለይም የተጎጂዎች ደምጽ የሚሰማበት መሆን ያስፈልጋል።

ተጠያቂነት፣ እርቅ እና መግባባት ማምጣት በኢትዮጵያ ለዓመታት የቆየውን የጥቃት አዙሪት ለመስበር ቁልፍ ነው፤ አሜሪካ በዚህ ሂደት አጋር ትሆናለች። "

በሌላ በኩል ፦ የተባበሩት መንግሥታት የሰብአዊ መብቶች ምክር ቤት በጦርነቱ የተፈጸሙ ጥሰቶችን በሚያጣራው የሰብዓዊ መብቶች ባለሙያ ቡድን ዛሬ መጋቢት 12/ 2015 ዓ.ም ገለጻ ይቀርብለታል ተብሏል።

መረጃው የቢቢሲ አማርኛው አገልግሎት ነው።

@tikvahethiopia
#MoE

" የመውጫ ፈተናውን በተደጋጋሚ ወስዶ ማለፍ ያልቻለ ተማሪ ከዲግሪ በታች ባሉ ደረጃዎች ምዘና ወስዶ መቀጠል እንዲችል የሚያደርግ የብቃት ማረጋገጫ ማዕቀፍ እየተዘጋጀ ነው " - ትምህርት ሚኒስቴር

250 ሺ ለሚጠጉ የመጀመሪያ ዲግሪ ተመራቂዎች የዩኒቨርሲቲ መውጫ ፈተና ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል።

በመጪው #ሐምሌ_ወር ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በመጀመሪያ ዲግሪ ለሚመረቁ ተማሪዎች የመውጫ ፈተና ለመስጠት ዝግጅት እየተጠናቀቅ እንደሚገኝ በሚኒስቴሩ የከፍተኛ ትምህርት ጥራትና ብቃት ማሻሻያ ዴስክ ኃላፊ ሰይድ መሐመድ ለኢፕድ ተናግረዋል፡፡

የትምህርት ሚኒስቴር የመውጫ ፈተናውን በተሳካ ሁኔታ ለመስጠት ከመንግሥት እና ከግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጋር በቅርበት እየሠራ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡

የመውጫ ፈተናውን ወስደው ማለፍ ያልቻሉ ተማሪዎች ደጋግመው መፈተን የሚችሉበት ዕድል መኖሩን ኃላፊው አመልክተዋል።

ፈተናውን በተደጋጋሚ ወስዶ ማለፍ ያልቻለ ተማሪ ከዲግሪ በታች ባሉ ደረጃዎች ምዘና ወስዶ መቀጠል እንዲችል የሚያደርግ የብቃት ማረጋገጫ ማዕቀፍ በትምህርትና ሥልጠና ባለሥልጣን በመዘጋጀት ላይ ይገኛል ብለዋል።

ይሁን እንጂ ተፈታኙ ለዩኒቨርሲቲ መውጫ ፈተና ዝግጁ ነኝ ብሎ ባሰበ ጊዜ ፈተናውን መውሰድና ማለፍ ከቻለ የዲግሪ ማረጋገጫ ማግኘት እንደሚችል ገልጸዋል።

የመውጫ ፈተናው በ #ኦንላይን እንደሚሰጥ ያመለከቱት ኃላፊው፤ ለዚህ ያመች ዘንድም የሶፍትዌር ማዘጋጀትን ጨምሮ ፈተናውን በስኬት መስጠት የሚያስችሉ ሥራዎች በመሠራት ላይ ናቸው ብለዋል።

ተማሪዎች ዋናውን ፈተና ከመፈተናቸው በፊት ሞዴል ፈተናዎች እንደሚወስዱ ጠቅሰዋል፡፡ 

#ኢፕድ

@tikvahuniversity @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" ሁሉም ተፋላሚ ወገኖች የጦር ወንጀሎችን ፈፅመዋል " - አንቶኒ ብሊንከን አሜሪካ በትግራይ ተቀስቅሶ ወደ አማራ እና አፋር ክልሎች በተዛመተው ጦርነት ሁሉም ተፋላሚ ወገኖች የጦር ወንጀሎች ፈጽመዋል የሚል ድምዳሜ ላይ መድረሷን አሳውቃለች። ይህንን ያሳወቀችው ትላንት በውጭ ጉዳይ ቢሮዳ በኩል የአገራትን የሰብዓዊ መብቶች ይዞታን በተመለከተ የሚያደርገው ግምገማ ዓመታዊ ሪፖርት ይፋ ስታደርግ ነው። ሪፖርቱን…
#Update

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ፦

• " የኢትዮጵያ መንግሥት በአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መ/ቤት የቀረበበትን የሰብአዊ መብት ጥሰት ክስ በፍፁም አይቀበልም "

• " መግለጫው በሀገሪቱ አንድን ወገን በሌላኛው ላይ ለማነሣሣት ጥቅም ላይ ሊውል የሚችል ቆስቋሽ መግለጫ ነው "

የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት በሰሜን ኢትዮጵያ በተፈጠረው ጦርነት " ከፍተኛ የሰብአዊ መብት ጥሰት ተከስቷል " ሲል የደረሰበትን ድምዳሜ የኢትዮጵያ መንግሥት በፍፁም እንደማይቀበለው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ማስታወቁን የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ዘግቧል።

የኢፌዴሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዛሬ ባወጣው መግለጫ የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት ጉዳዩን በተመለከተ ያወጣው መግለጫ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን እና የተመድ የሰብአዊ መብት ኮሚሽነር በጋራ ካደረጉት ምርመራ አንፃር ሲታይ ምንም አዲስ ግኝት ያልተካተተበት ነው ብሏል።

በመሆኑም የኢትዮጵያ መንግሥት ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ያቀረበበትን ባዶ ውግዘት #በፍፁም እንደማይቀበለው ገልጿል።

የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት ያወጣው መግለጫ አንድን ወገን ብቻ መወንጀል ላይ ያነጣጠረ መሆኑንም ነው ሚኒስቴሩ የጠቆመው።

በሌላ በኩል ኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አማራጮችን ለመለየት ብሔራዊ ምክክር ለመጀመር በተዘጋጀችበት ወቅት ላይ የወጣ በመሆኑም መግለጫው ወቅቱን ያልጠበቀ ነው ብሎታል።

በተጨማሪም የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት ይህን መግለጫ ለማውጣት ያሰበበት ዓላማ ምንም ይሁን ምን መግለጫው በሀገሪቱ አንድን ወገን በሌላኛው ላይ ለማነሣሣት ጥቅም ላይ ሊውል የሚችል ቆስቋሽ መግለጫ ነው ሲል ገልጾታል።

@tikvahethiopia
#PMOEthiopia

ዛሬ ማክሰኞ የሚኒስትሮች ምክር ቤት 18ኛ መደበኛ ስብሰባ አካሂዶ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ውሳኔ አሳልፏል።

ም/ቤቱ ከተወያየባቸው ጉዳዮች አንዱ የኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን ማቋቋሚያ ደንብ ለማሻሻል በቀረበ ረቂቅ ደንብ ላይ ነው።

የኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን የተፈቀደ እና የተከፈለ ካፒታል በማሻሻል የተቋቋመበትን ዓላማና ተልዕኮ ለማሳካት እንዲችል በተለይ ፦

- በግንባታ ላይ ያሉ የባቡር መሰረተ ልማቶች እንዲጠናቀቁ የተጠናቀቁትም ወደ ስራ እንዲገቡ፤

- በቀጣይ ለሚገነቡ የባቡር መሠረተ- ልማቶች የተሻለ አቅም እንዲኖረው የተፈቀደ ካፒታሉ ወደ ብር 221 ቢሊዮን ከፍ እንዲል በጥሬ ገንዘብና በአይነት የተከፈለ ካፒታሉ ደግሞ ብር 120 ቢሊዮን እንዲሆን ረቂቅ ደንብ ተዘጋጅቶ መቅረቡ ተገልጿል።

ምክር ቤቱም በረቂቅ ደንቡ ላይ ተወያይቶ ግብዓቶችን በማከል በነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በስራ ላይ እንዲውል በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡

(ተጨማሪ የዛሬ የምክር ቤቱን ወሳኔዎች ከላይ ያገኛሉ)

@tikvahethiopia
#ቭላድሚር_ፑቲን

የሩስያ ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን አገራቸው ሩስያ ከአፍሪካ ጋር ላላት ግንኙነት ቅድሚያ እንደምትሰጥ ተናገሩ።

ይህን ያሉት ትናንት ሰኞ ሞስኮ ውስጥ መካሄድ በጀመረውና ከ40 በላይ የአፍሪካ ሀገራት ልዑካን እየተካፈሉበት እንዳሆነ በተነገረው የሩሲያ-አፍሪካ ጉባኤ ላይ ነው።

ፕሬዜዳንት ፑቲን ምን አሉ ?

" አገራችን ከአፍሪካ አገራት ጋር ለመተባበር ቅድሚያ እንደምትሰጥ እና በዚህም እንደምትቀጥል አጽንኦት መስጠት እፈልጋለሁ።

ከዩክሬን በሚቀርበው እህል ላይ የተደረሰው ስምምነት ካልታደሰ ሩሲያ ለተቸገሩ የአፍሪካ አገራት #በነጻ እህል ታቀርባለች።

በባለፉት ዓመታት ሲላክ የነበረውን የእህል መጠን ለአፍሪካ አገራት በተለይም ከሩሲያ ለሚፈልጉ በነጻ ለማቅረብ ዝግጁ ነን።

ሩሲያ የደረሰችባቸውን የቴክኖሎጂ ውጤቶች ለአፍሪካ አገራት ታካፍላለች ፤ የኤሌክትሪክ ሀይል እንዲያመርቱ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ ትቀጥላለች።

አፍሪካ እያቆጠቆጠ ባለው የብዝኃ የዓለም ስርዓት ላይ ስልጣኗን እና ሚናዋን ማሳደግ እንደምትቀጥል አምናለሁ። "

#BBC

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#አፋልጉን በአዲስ አበባ ሳሪስ አዲስ ሰፈር በቤት ሰራተኝነት ተቀጥራ ትሰራ የነበረች " ቤዛዊት በቀለ " የምትባል ሞግዚት / ግለሰብ ከምትሰራበት ቤት የ2 ዓመት ህጻን የሆነችውን ሶልያና ዳንኤልን (ከላይ በፎቶ ተያይዟል) ከቤት ይዛት መሰወሯን ቤተሰቦቿ ገልጸውልናል። እናት እና አባትን ጨምሮ መላው ቤተሰብ ጭነቅት ላይ የሚገኙ ሲሆን የንፋስ ስልክ ፖሊስ መምሪያ ጉዳዩን እንዲያውቀው ተደርጓል። ህፃን…
#Update

ህፃን ሶሊያን ዳንኤል ተገኝታለች።

• " 40 ሺህ ብር ይከፈልሻል ብለው ሰዎች ስላግባቧት ህፃኗን ሰርቃ ልትሰወር መቻሏል ተጠርጣሪዋ ገልጻለች " - የአዲስ አበባ ፖሊስ

ከቀናት በፊት በሞግዚቷ ተሰርቃ የተወሰደችው የ2 ዓመቷ ህፃን ሶሊያና ዳንኤል ከብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ጋር በመተባበር ባደረገው ጠንካራ ክትትል ሱሉልታ ከተማ ላይ መገኘቷን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል።

የሁለት (2) ዓመት ዕድሜ ያላት ህፃን ሶሊያና ዳንኤል ሳሪስ አዲስ ሰፈር ተብሎ ከሚጠራው አካባቢ ሃሙስ መጋቢት 7 ቀን 2015 ዓ/ም ረፋድ ላይ ቤዛ በቀለ በተባለችው የቤት ሰራተኛቸው ተሰርቃ ስለመወሰዷ ይህን ተከትሎ የወላጆቿ የአፋልጉን ጥሪ ሲሰራጭ መቆየቱ ይታወሳል፡፡

የአዲስ አበባ ፖሊስ በህፃኗ ወላጆች የቀረበለትን አቤቱታ ተቀብሎ ከብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ጋር በመቀናጀትና ከአዲስ አበባ ውጪ ወደተለያዩ የሃገራችን ከተሞች እና አካባቢዎች በመሄድ ጭምር አስፈላጊ መረጃዎችን በፖሊሳዊ ጥበብ በማሰባሰብ ከፍተኛ ጥረትን የጠየቀ ክትትል ሲያደርግ መቆየቱን ገልጿል።

" የክትትል ስራው ቀንና ሌሊት ደጅ ውሎ ማደርን የግድ የሚል እጅግ አድካሚ  ነበር " ያለው ፖሊስ " በስተመጨረሻም ቤዛ በቀለ ዛሬ መጋቢት 12 ቀን 2015 ዓ/ም ሱሉልታ ከተማ "ኖኖ መና አቢቹ" ተብሎ በሚጠራው ቀበሌ በአንድ መኖሪያ ቤት ውስጥ ህፃን ሶሊያና ዳንኤልን ሸሽጋ በተቀመጠችበት  በቁጥጥር ስር መዋሏን አሳውቋል።

ተጠርጣሪዋ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ከዋለች በኋላ እንደተናገረቸው 40 ሺህ ብር ይከፈልሻል ብለው ሰዎች ስላግባቧት ህፃኗን ሰርቃ ልትሰወር ችላለች፡፡

በወንጀሉ ላይ ተሳትፎ አላቸው የተባሉ ሌሎች ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር ለማዋል ምርመራው መቀጠሉን የአዲስ አበባ ፖሊስ ገልጿል፡፡

#AddisAbabaPolice

@tikvahethiopia