TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#AddisAbaba

71 ሺ 832 ተማሪዎች የሚፈተኑበት የዘንድሮው የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና ሰኔ 27 ይጀምራል።

የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና ከሰኔ 27 እስከ 29 እንደሚሰጥ የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ አስታወቀ።

የቢሮው ምክትል ሃላፊ አቶ ዳኘው ገብሩ በፈተናው አሰጣጥ ዙሪያ መግለጫ ሰጥተዋል።

በመግለጫው የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና በከተማዋ በ 792 ትምህርት ቤቶች እንደሚሰጥ ተነግሯል።

ለዚህም 179 የመፈተኛ ጣቢያዎች ተዘጋጅተዋል ብለዋል ።

አቶ ዳኘው አክለውም አጠቃላይ በከተማዋ 71 ሺህ 832 ተማሪዎች እንደሚፈተኑ ነው የተናገሩት።

ኮማንድ ፖስት ተቋቁሞ እስካሁን ያለውን የፈተናው ዝግጅት ሂደት የገመገመ ሲሆን ፈተናው ወደ መፈተኛ ጣቢያዎች ለማጓጓዝ ሂደት ላይ ነውም ተብሏል።

ሰኔ 24 ቀንም ለሁሉም ፈተናውን ለሚመለከት የትምህርት ማህበረሰብ ኦረንቴሽን እንደሚሰጥም ተገልጿል፡፡

(አዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ)

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Ethiopia #Sudan

የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ የኢትዮጵያ እና ሱዳንን ወቅታዊ ሁኔታ በተመለከተ በአረብኛ ቋንቋ ባሰራጩት መልዕክት የሱዳንና የኢትዮጵያ ህዝቦች ወንድማማቾች መሆናቸውን ገልፀው በሁለቱ ሀገራት መካከል ችግር መኖሩ ግልፅ ነው ብለዋል።

ነገር ግን ሁለቱ ሀገራት እነዚያን ችግሮች ለመፍታት ሊጥሩ እና ሊተባበሩ ይገባል ሲሉ ገልፀዋል።

ኢትዮጵያ እና ሱዳንን ለማጋጨት የሚፈልጉ መንግስታት ወይም #ሌሎች_ወገኖች ቢኖሩም እነዚህ አካላት ከሁለቱ ሀገራት ህዝቦች ግጭት የሚያተርፉት አይኖርም ሲሉ አስረድተዋል።

#በውጭ_ሀይል_ግፊት በሁለቱ ሀገራት መካከል ውዝግብ ሊኖር እንደማይግባ ገልፀው ራሳችንን ልንቆጣጠር እና ከግጭት ልንቆጠብ ይግባል ብለዋል።

" በመካከላችን የጠላትነት መንፈስ ሊኖር አይግባም ፤ ይልቁንም በልማት ልንተባበር እና አብረን ልናድግ ይገባናል " ሲሉ ገልፀዋል።

ለሱዳን ህዝብ ክብር አለን ያሉት ዶ/ር ዐቢይ የሁለቱ ሀገራት ህዝቦች ያጋጠማቸውን ችግር በወንድማማችነትና በመልካም ጉርብትና መንፈስ የመፍታት አቅም አላቸው ብለዋል።

በሌላ በኩል ፤ ትላንት የሱዳን ሉዓላዊ የሽግግር ም/ቤት ሊቀ መንበር አብዱል ፋታህ ከአውሮፓ ሕብረት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ አኔቴ ዌበር ጋር ካርቱም ውስጥ ተወያይተው ነበር ፤ በዚህም ወቅት ቡርሃን " ከኢትዮጶያ ጋር ጤናማ ግንኙነት እንዲኖረን እንፈልጋለን " ማለታቸውን ሱና ዘግቧል።

የአውሮፓ ህብረት በኢትዮጵያ እና ሱዳን መካከል ያለውን አለመግባባት ለማርገብ ጥረት እያደረገ መሆኑ ተነግሯል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update ለአንድ ዓመት ጊዜ ዝግጅት ተደርጎበታል የተባለው የመጀመሪያው የሃጫሉ ሁንዴሳ አዋርድ ሰኔ 22 ይካሄዳል። የሃጫሉ ሁንዴሳ ፋውንዴሽን ዛሬ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል። ሰኔ 22 በሚካሄደው መጀመሪያው ዙር የሽልማት መርሐግብር አርቲስት ሀጫሉ ሁንዴሳ ከተገደለ ጀምሮ እስከ ዓመት ከስምንት ወር ያሉ የአፋን ኦሮሞ ሙዚቃዎችን ለመሸለም የታቀደ መሆኑን ባለቤቱ ወ/ሮ ፋንቱ ደምሰው ተናግረዋል። ሰኔ…
ፎቶ፦ ዛሬ ሰኔ 22 ቀን 2014 የአርቲስት ሀጫሉ ሁንዴሳ የመጀመሪያ አዋርድ እየተካሄደ ይገኛል።

በስነስርዓቱ ላይ ቤተሰቦቹን ጨምሮ የውድድሩ እጩዎች እንዲሁም በርካታ ተጋባዥ እንግዶች ተገኝተዋል።

ስነስርዓቱ የተጀመረው አርቲስት ሀጫሉ ሁንዴሳን በማሰብ ሲሆን ቤተሰቦቹን ጨምሮ በአዳራሹ የተገኙ እንግዶች በከፍተኛ ሀዘን ውስጥ ሆነው ሲያለቅሱ ተስተውሏል።

የሀጫሉ ሁንዴሳ አዋርድ ሁሌ በየዓመቱ ሰኔ 22 የሚቀጥል ሲሆን በሀጫሉ ሁንዴሳ ፋውንዴሽን በኩል የሚዘጋጅ ነው።

(Tikvah Family)

Tikvah Ethiopia AFAAN OROMOO
https://publielectoral.lat/+UTMftkYHBuOGaQ23

@tikvahethiopia
#EHRC

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ፤ ከግንቦት 15 እስከ 20/2014 ዓ.ም በአፋር ክልል ሰመራ ከተማ በሚገኙ ሰመራ እና አጋቲና ካምፖች በመባል በሚታወቁ ቦታዎች ውስጥ ከሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ጋር ተያይዞ " ለደኅንነታቸው ጥበቃ እና በወንጀል ጥርጣሬ የሚፈለጉ ሰዎችን ለመለየት " በሚል ምክንያት ከትግራይ ክልል አዋሳኝ ከሆኑ 3 የአፋር ክልል ወረዳዎች ፦
- ከአባላ
- ከኮነባ
- ከበረሃሌ በታኅሣሥ ወር 2014 ዓ/ም ተይዘው የቆዩና በሁለቱ ካምፖች የሚገኙ ወደ 9,000 የሚጠጉ የትግራይ ተወላጆች ያሉበትን ሁኔታ በቦታው በመገኘት፣ በማነጋገር፣ የመንግሥት አካላትና አገልግሎት ሰጪዎችን እንዲሁም ሌሎች መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችን በማነጋገር ክትትል ሲያደርግ መቆየቱን ገልጿል።

ኮሚሽኑ ያነጋገራቸው በካምፖቹ ውስጥ የሚገኙት ሰዎች ከመኖሪያቸው አካባቢ እንዲወጡና በነዚህ ቦታዎችም እስካሁንም ድረስ እንዲቆዩ የተደረጉት ከፍቃዳቸው ውጪ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ 

በካምፖቹ የሰብአዊ እርዳታና የሕክምና አገልግሎት አቅርቦት እጅግ ውስን በመሆኑና በካምፑ በተከሰተ ወረርሽኝ መሰል በሽታ #ለሕይወት_መጥፋት ጭምር ምክንያት ሆኗል፡፡

በወሊድ ምክንያት ካልሆነ በስተቀር በአካባቢው ወደሚገኝ የጤና ተቋም ሄዶ ለመታከም ባለመፈቀዱ ሁኔታውን አስቸጋሪ አድርጎታል።

ባለፉት አምስት ወራት ሰመራ ካምፕ ብቻ በበሽታ ሕይወታቸው ያለፉ ሰዎች እና ካምፑ ውስጥ በወሊድ ወቅት ልጅ የሞተባት እናት መኖራቸውን ተይዘው የሚገኙት ሰዎች አስረድተዋል።

ዶ/ር ዳንኤል በቀለ ፤ በካምፕ ውስጥ ተይዘው የሚገኙት ሰዎች ሁኔታ በመጠለያ ጣቢያ ስም የተፈጸመ፣ በብሔር ማንነት ላይ የተመሰረተ ሕገ ወጥ እና የዘፈቀደ እስር በመሆኑ በአፋጣኝ ሊለቀቁ ይገባል ብለዋል፡፡

(ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Ethiopia #Sudan የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ የኢትዮጵያ እና ሱዳንን ወቅታዊ ሁኔታ በተመለከተ በአረብኛ ቋንቋ ባሰራጩት መልዕክት የሱዳንና የኢትዮጵያ ህዝቦች ወንድማማቾች መሆናቸውን ገልፀው በሁለቱ ሀገራት መካከል ችግር መኖሩ ግልፅ ነው ብለዋል። ነገር ግን ሁለቱ ሀገራት እነዚያን ችግሮች ለመፍታት ሊጥሩ እና ሊተባበሩ ይገባል ሲሉ ገልፀዋል። ኢትዮጵያ እና ሱዳንን ለማጋጨት የሚፈልጉ…
#Update #Ethiopia #Sudan

" መረጃው ውሸት ነው " - ዶ/ር ለገሰ ቱሉ

" በእግረኛ የሚመጡ ከሆነ የአካባቢው ታጣቂ በተጠንቀቅ ቆሟል " - አቶ አብራራው ተስፋ

" ሱዳን ትሪቡን " የተባለው የሱዳን ሚዲያ የሱዳን ጦር ሰራዊት ባለፈው ሳምንት በኢትዮጵያ ኃይሎች ተወሰደብኝ ያለውን እርምጃ ለመበቀል የይገባኛል ጥያቄ በሚናሳበት የአልፋሽጋ አካባቢ ቀደም ሲል በኢትዮጵያ ስር የነበሩ " ካላ ላባን " እና " በረከት " የተባሉ አካባቢዎችን ተቆጣጥሯል ሲል ዘግቧል።

በዘገባውም ላይ የሱዳን ጦር በርካታ የኢትዮጵያ የጦር ተሸከርካሪዎች ላይ ጉዳት እንዳደረሰ  / እንዳቃጠለ ፣ ወታደሮችንም እንደማረከ ገልጿል።

ዛሬ ለዶቼ ቨለ ሬድዮ ጣቢያ ቃላቸውን የሰጡት የኢፌድሪ የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስተር ዶ/ር ለገሰ ቱሉ መረጃው #ውሸት እንደሆነ አረጋግጠዋል።

በሌላ በኩል በም/ጎንደር ዞን ምዕራብ አርማጭሆ ወረዳ የሱዳን ጦር አካባቢው እንዳይለማ አልሞ አሁንም ድረስ ከእርቀት መድፍ እየተኮሰ እንደሆነ የወረዳው የሰላምና ደህንነት ኃላፊ አቶ አብራራው ተስፋ ለሬድዮ ጣቢያው በሰጡት ቃል ገልፀዋል።

አንድ የአካባቢው ነዋሪም የሱዳን ጦር ትንኮሳውን በአካባቢው ትናንት ማምሻውን ቀጥሎ እንደነበር አስረድተዋል፡፡ 

መድፍ ከእርቀት ከመተኮስ ያለፈ ነገር እንደሌለ የሚናገሩት የወረዳው የሰላምና ደህንነት ኃላፊ ፥ " በእግረኛ የሚመጡ ከሆነ የአካባቢው ታጣቂ #በተጠንቀቅ_ቆሟል ነው " ያሉት፡፡ 

ህብረተሰቡ በሚተኮሱት ከባባድ መሳሪያዎች ከመደናገጥ ይልቅ ተደራጅቶ ዘልቀው የሚመጡ ከሆነ እየጠበቀ እንደሆነ ነው ለሬድዮ ጣቢያው ያስረዱት፡፡

@tikvahethiopia
#ZH

ያገለገሉ እና አዲስ ካሜራ እና የካሜራ እቃዎችን እንገዛለን እንሸጣለን ከታች ባለው ቴሌግራም ሊንክ ያገኙ https://publielectoral.lat/joinchat/AAAAAEUTeB3LSYVFukiuQw

ይደውሉልን 0911284905

አድራሻ= ቦሌ ወሎ ሰፈር HMM ህንፃ 2ኛ ፍቅ 205
#Sudan #June30March

ዛሬ በሱዳን ከፍተኛ ተቃውሞ ይካሄዳል ተብሎ ይጠበቃል።

ዛሬ #June30 በጎረቤት ሱዳን በሌ/ጄነራል አብዱል ፈታህ አል ቡርሃን የሚመራውን ወታደራዊ ጁንታን በመቃወም ከፍተኛ የሆነ የተቃውሞ ሰልፍ ይካሄዳል ተብሎ ይጠበቃል።

በተቃውሞ ሰልፉ ወታደራዊው ክንፍ በመፈንቅለ መንግስት የያዘውን ስልጣን ለሲቪል አስተዳደር እንዲያስረክብ እና የሲቪል መንግስት እንዲቋቋም ይጠየቅበታል ነው የተባለው።

ተቃውሞውን ተከትሎ የፀጥታ ኃይሎች የተለያዩ መንገዶችን ዘግተዋል። በተጨማሪ የፀጥታ ኃይሎች ሰልፍ የሚያስተባብሩትን አክቲቪስቶች እያደኑ እያሰሩ ነው ተብሏል።

የሱዳን ወታደራዊ ክንፍ በመፈንቅለ መንግስት ስልጣን ከተቆጣጠረ በኃላ በሱዳን ዜጎች የሚደርስበት ተቃውሞ እስካሁን የቀጠለ ሲሆን ስልጣኑን ለሲቪል አስተዳደር እንዲያስረክብ ግፊት እየተደረገበት ይገኛል።

እስከዛሬ ድረስ በነበሩት ተቃውሞዎች የመንግስት ፀጥታ ኃይሎች በወሰዷቸው እርምጃዎች ብዙ ሰዎች ሞተዋል፤ በርካቶችም ቆስለዋል።

@tikvahethiopia