TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን በተለያዩ ፖሊስ መምሪያዎች በእስር ላይ ያሉ የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) አባሎች የእስር ሁኔታን በተመለከተ ለረጅም ጊዜ ክትትል ሲያደርግ ነበር።

በተጨማሪ ከፓርቲውና ከእስረኞች ቤተሰቦች በቀረቡ አቤቱታዎች መነሻነት ከመጋቢት 1 እስከ 10 / 2014 ዓ/ም በቡራዩ ከተማ፣ በገላን ከተማ እና በሰበታ ፖሊስ መምሪያዎች በአካል በመገኘት ክትትል በማድረግ እስረኞችን፣ የፖሊስ መምሪያ ኃላፊዎችን፣ የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽንን እና የኦሮሚያ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ተወካዮችን በማነጋገር ምርመራ አድርጓል። 

ኢሰመኬ በቡራዩ ፖሊስ መምሪያ በእስር ላይ የነበሩ፦

➡️ አቶ ሚካኤል ጎበና
➡️ አቶ ኬኔሳ አያና
➡️ ዶ/ር ገዳ ወልጅራ
➡️ አቶ ዳዊት አብደታ
➡️ አቶ ለሚ ቤኛ
➡️ አቶ ገዳ ገቢሳ የተባሉ የፓርቲው አመራር መሆናቸውን የገለጹ ስድስት እስረኞችን አነጋግሯል።

በተጨማሪ ኮሎኔል ገመቹ አያና በፌደራል ፖሊስ የወንጀል ምርመራ ማዕከል/እንዲሁም አቶ አብዲ ረጋሳ ገላን ከተማ በሚገኘው የኦሮሚያ ክልል ልዩ ፖሊስ ካምፕ ውስጥ በእስር ላይ የሚገኙ መሆኑን ከቤተሰብና ከጠበቆቻቸው መረዳት ተችሏል፡፡

በዚህ ምርመራ መሰረት፣ ፍ/ቤት በዋስትና እንዲለቀቁ የፈቀደላቸው፣ የክስ መዝገቦቻቸው ተዘግተው በፍርድ ቤት ውሳኔ በነፃ የተሰናበቱ፣ ምንም አይነት ክስ ያልተመሰረተባቸውና ዐቃቤ ሕግ ክስ የማይመሰርትባቸው መሆኑን በማረጋገጥ የምርመራ መዝገባቸው የተዘጋ፤ሆኖም ከወራት እስከ 2 ዓመት ለሚሆን ጊዜ በተለያዩ ቦታዎች እየተዘዋወሩ ከሕግ አግባብ ውጪ በእስር ላይ የሚገኙና የተወሰኑትም በእስሩ ሂደት በተፈጸመ ተገቢ ያልሆነ አያያዝ እና ድብደባ ለተለያዩ የአካል ጉዳቶችና የጤና እክል የተጋለጡ እስረኞች መሆናቸውን ኢሰመኮ ተረድቷል።

(ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን በተለያዩ ፖሊስ መምሪያዎች በእስር ላይ ያሉ የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) አባሎች የእስር ሁኔታን በተመለከተ ለረጅም ጊዜ ክትትል ሲያደርግ ነበር። በተጨማሪ ከፓርቲውና ከእስረኞች ቤተሰቦች በቀረቡ አቤቱታዎች መነሻነት ከመጋቢት 1 እስከ 10 / 2014 ዓ/ም በቡራዩ ከተማ፣ በገላን ከተማ እና በሰበታ ፖሊስ መምሪያዎች በአካል በመገኘት ክትትል በማድረግ እስረኞችን፣…
#OLF

የኢሰመኮ ዋና ኮሚሽነር ዶ/ር ዳንኤል በቀለ ፦

" የኦነግ ፓርቲ አመራሮች ለተራዘመ ጊዜ ከሕግ አግባብ ውጭ ታስረው የሚገኙ በመሆኑ በአፋጣኝ ከእስር ሊለቀቁ እና ለደረሰባችው ጉዳት ሊካሱ ይገባል።

በተጨማሪ የፍርድ ቤትና የዐቃቤ ሕግ ውሳኔዎች በተደጋጋሚ እየተጣሰ እስረኞቹ ከሕግ ውጪ ለተራዘመ እስር መዳረጋቸው ስልጣንን ያለአግባብ መጠቀም ስለሆነ የኦሮሚያ ክልል መንግሥት አፋጣኝ ማጣራት አካሂዶ ተገቢውን እርምጃ ሊወሰድበት ይገባል "

▪️

የኢሰመኮ የሲቪል፣ ፖለቲካ፣ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ መብቶች ኮሚሽነር ዶ/ር አብዲ ጂብሪል ፦

" ታሳሪዎቹ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች በመሆናቸው በሕዝባዊ አገልግሎት ስራቸው ለሰብአዊ መብቶች ጥሰት እንዳይጋለጡ ጥበቃ ሊደረግ ሲገባ፤ በተግባር የተገላቢጦሽ መሆኑ አሳዛኝ ነው ጉዳዩ አፋጣኝ እልባት ያስፈልገዋል "

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#UPDATE በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በዓመት ሁለት ጊዜያት ከሚካሄዱት የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤያት አንዱ የርክበ ካህናት ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ (የ2014 ዓ/ም) መካሄድ ጀምሯል። ጉባኤውን አስመልክቶ ፥ አባ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት መልዕክት አስተላልፈዋል። በመልዕክታቸው ፤ ጉባኤው…
#Update

የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ሀገራዊ ሰላም በተመለከተ ተወያይቶ ውሳኔ በማስተላለፍ ውሳኔውን የሚያስፈጽሙ አባቶችን ሰይሟል።

የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ 23 የመወያያ አጀንዳዎችን አጽድቆ በመወያየት ልዩልዩ ውሳኔዎችን ማስተላለፍ ጀምሯል።

ዓመታዊው የግንቦቱ የቅዱስ ሲኖዶስ ርክበ ካህናት ጉባኤ ግንቦት 9 ቀን 2014 ዓ.ም በጸሎት ከተጀመረ በኋላ በትላንትናው ዕለት በጠዋቱ መርሐ ግብር የቅዱስነታቸውን የመክፈቻ መልዕክት አዳምጧል።

በመቀጠልም ሰባት አባቶችን የያዘ የአጀንዳ አርቃቂ ኮሚቴ አባላትን በመሰየም አጀንዳዎችን አዘጋጅተው እንዲያቀርቡ ካደረገ በኋላ በኮሚቴው ተዘጋጅተው የቀረቡለትን አጀንዳዎች መርምሮ ማስተካከያ ካደረገባቸው በኋላ አጽድቋቸዋል።

በመቀጠልም በአጀንዳዎቹ ቅደም ተከተል መሰረት የቅዱስነታቸውን የመክፈቻ መልዕክት ያጸደቀ ሲሆን ሀገራዊ ሰላም በተመለከተ ተወያይቶ ውሳኔ በማስተላለፍ ውሳኔውን የሚያስፈጽሙ አባቶችን ሰይሟል።

የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ በዛሬ ጠዋት የጉባኤ ውሎው ልዩ ልዩ ውሳኔዎችን እንደሚያስተላልፍ የሚጠበቅ ሲሆን ከሰዓት በኋላን ጨምሮ እስከ እሁድ ድረስ በበዓላት ምክንያት ጉባኤው እንደማይካሔድ ታውቋል።

ምልዐተ ጉባኤው ከሰኞ ጠዋት ጀምሮ መደበኛ ስብሰባውን በማከናወን ቀሪ አጀንዳዎችን መሰረት ያደረጉ ውሳኔዎችን ያስተላልፋል ተብሎ ይጠበቃል።

ምንጭ፦ የኢኦተቤ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ

@tikvahethiopia
#አቢሲኒያ_ባንክ

በአቢሲንያ የኢ-ኮሜርስ ክፍያ መንገድ ንግድዎን ያቀላጥፉ !

የድርጅትዎን ድህረ ገፅ ወይም መተግበሪያ ከባንካችን የኢ-ኮሜርስ ክፍያ መንገድ ጋር በማሳለጥ ከመላው ዓለም ክፍያ በቪዛ እና ማስተር ካርድ በቀላሉ መቀበል ይችላሉ።
የአቢሲንያ ባንክን ትክክለኛ የቴሌግራም ቻናል ይቀላቀሉ! https://publielectoral.lat/BoAEth
#ኮሎኔል_ገመቹ_አያና

➡️ " ኮሎኔል ገመቹ አያናን ከኦሮሚያ ፖሊስ በአደራ ከመቀበል ውጪ ምንም የወንጀል የምርመራ መዝገብ በስማቸው የለንም ፤... ኮለኔል ገመቹን ይዘን ወደ ኦሮሚያ ፖሊስ በመሔድ ተረከቡን ብለን ስንጠይቅ ኦሮሚያ ፖሊስ እኛ ጋር ጉዳይ የለውም የሚል ምላሽ ሰጥቶናል " - ኮማንደር ኤርትሮ ኦቦ ከፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን

➡️ " ኮ/ል ገመቹ መታሰራቸውን አንፈልግም ቢለቀቁ አልቃወምም " - አቃቤ ህግ

➡️ " ፍርድ ቤት ነጻ እንዳለኝ ሁሉ በነጻ እንድፈታ እፈልጋለሁ "  - ኮሎኔል ገመቹ አያና

ፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ኮ/ል ገመቹ አያናን ከኦሮሚያ ፖሊስ በአደራ ከመቀበል ውጪ ምንም የወንጀል የምርመራ መዝገብ በስማቸው እንደሌለው ገልጿል።

የኦነግ ከፍተኛ አመራር የሆኑት ኮሎኔል ገመቹ አያና ባለፈው ዓመት ግንቦት 9/ 2013 ዓ/ም በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 3ኛ የፀረሽብርና ህገመንግስታዊ ወንጀል ችሎት ከተከሰሱበት የሽብር ወንጀል በነጻ መሰናበታቸው ይታወሳል።

ሆኖም በነጻ ከተሰናበቱ በኋላ በነጋታው ግንቦት 10 ቀን 2013 ዓ/ም ከቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ሲወጡ በር ላይ በኦሮሚያ ፖሊስ ተይዘው መወሰዳቸውን እና 6 ወር በገላን ፖሊስ ጣቢያ እና ወታደራዊ ካንፕ እንዲሁም በአዋሽ መልካሳ በአንድ ጄነራል ዶሮ እርባታ ውስጥ ታስረው እንደነበር እና ከህዳር 16 ቀን 2014 ዓ/ም ጀምሮ ደግሞ ለፌደራል ፖሊስ ተላልፈው እንደተሰጡና እንደታሰሩ ተገልጾ ነበር።

ያንብቡ ; https://telegra.ph/Tarik-Adugna-05-19

Credit : ጋዜጠኛ ታሪክ አዱኛ

@tikvahethiopia
#Update

ኢንዶኔዥያ በሀገር ውስጥ #የምግብ_ዘይት አቅርቦት ላይ መሻሻሎች መታየቱን ተከትሎ እ.ኤ.አ. ከሰኞ ግንቦት 23 /2022 ጀምሮ የፓልም ዘይት ወደ ውጭ እንዳይላክ የተጣለው እገዳ እንደሚነሳ ፕሬዝዳንት ጆኮ ዊዶዶ በዛሬው ዕለት ተናግረዋል።

@tikvahethiopia
#Qatar2022

በዓለም ዋንጫ ላይ አፍሪካን ወክለው የሚሳተፉ ዳኞች ይፋ ሆኑ።

በኳታር አዘጋጅነት በ 2022 ለሚካሄደው የአለም ዋንጫ ፊፋ 36 ዋና ዳኞችን 69 ረዳት ዳኞችን እና 24 የቫር ዳኞችን ውድድሩን እንዲመሩ መሾሙን አስታውቋል ።

ኢትዮጵያዊው ኢንተርናሽናል ዋና ዳኛ ባምላክ ተሰማ ፊፋ የአለም ዋንጫን እንዲመሩ ከሾማቸው ዳኞች ስም መካከል #አለመካትቱ ታውቋል ።

ፊፋ ለመጀመሪያ ጊዜ በኳታር አዘጋጅነት በሚካሄደው የአለም ዋንጫን ላይ ሶስት ዋና ሴት ዳኞችን እና ሶስት ረዳት ሴት ዳኞችን ውድድሩን እንዲመሩ መምረጡ ተገልጿል ።

የአለም ዋንጫን ለመጀመሪያ ጊዜ እንዲመሩ ከተመረጡ ሶስት ሴት ዳኞች መካከል አንዷ ሩዋንዷዊቷ ሳሊማ ሙካንሳንጋ መሆኗ ተዘግቧል ።

አፍሪካን ወክለው የአለም ዋንጫን እንዲመሩ የተመረጡ ስድስት ዋና ዳኞች ሳሊማ ሙካንሳንጋ ፣ ጃኒ ሲካዝዌ ፣ ባካሪ ጋሳማ ፣ ቪክቶር ጎሜዝ ፣ ማጉዬቴ ኒዳዬ እና ሙስጣፋ ጎርባል መሆናቸው ተነግሯል ።

More : @tikvahethsport
#የተመድ_ማስጠንቀቂያ

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሩስያ እና ዩክሬን ጦርነት በቀጣይ ወራት ዓለም አቀፍ የምግብ እጥረት ሊያስከትል እንደሚችል አስጠንቅቋል።

ዋና ጸሐፊው አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ትላንት በኒውዮርክ ንግግር ሲያደርጉ እንዳሉት ጦርነቱ በድሃ ሃገራት የዋጋ ንረትን በማስከተል የምግብ ዋስትና እጥረትን አባብሶታል።

የዩክሬን ወጪ ንግድ ከጦርነቱ በፊት ወደነበረበት ደረጃ ካልተመለሰ ዓለም ለዓመታት የሚዘልቅ ረሃብ ሊገጥማት ይችላል ብለዋል።

በአንድ ወቅት ከፍተኛ መጠን ያለው የሱፍ ዘይት፣ በቆሎ እና ስንዴ ወደ ውጭ ይልኩ የነበሩት የዩክሬን ወደቦች ከስራ ርቀዋል።

ይህም የዓለም አቀፍ አቅርቦትን ከመቀነስ ባለፈ የሌሎች አማራጮችን ዋጋ እንዲንር አድርጓል።

እንደ ተመድ መረጃ የዓለም የምግብ ዋጋ ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር በ30 በመቶ ብልጫ አለው።

ጉተሬዝ ፤ " ተባብረን ከሠራን በዓለማችን ላይ በቂ ምግብ አለ። ያለድን ችግር ዛሬ ካልፈታን በሚቀጥሉት ወራት በዓለም አቀፍ ደረጃ የምግብ እጥረት ችግር ውስጥ እንገባለን" ብለዋል።

የዩክሬን የምግብ ምርት እንዲሁም የሩሲያ እና የቤላሩስ #ማዳበሪያ ወደ ዓለም አቀፍ ገበያ ከመቀላቀል ውጭ ለምግብ ቀውሱ ምንም አይነት ውጤታማ መፍትሄ የለም ሲሉ አስጠንቅቀዋል።

የምግብ ምርቶችን ወደ መደበኛ ደረጃ ለመመለስ ከሩሲያ፣ ከዩክሬን፣ ከአሜሪካ እና ከአውሮፓ ህብረት ጋር "ጠንካራ ግንኙነት" እያደረጉ መሆናቸውን ተናግረዋል ።

በሌላ በኩል ፤ የዓለም ባንክ የምግብ ዋስትና እጦትን ለሚፈቱ ፕሮጀክቶች የሚውል 12 ቢሊዮን ዶላር ተጨማሪ የገንዘብ ድጋፍ ይፋ ማድረጉን አሳውቋል። እርምጃው በሚቀጥሉት 15 ወራት ለተመሳሳይ ፕሮጀክቶች ያለውን ጠቅላላ ገንዘብ ወደ ከ30 ቢሊዮን ፓውንድ በላይ ያደርሰዋል መባሉን ቢቢሲ ዘግቧል።

@tikvahethiopia
" እርምጃ ተወስዶባቸዋል "

በምዕራብ ጎንደር ዞን መተማ ወረዳ ሰው በማገት ፣ ሰው በመግደል ሲፈለጉ የነበሩ 3 ግለሰቦች እርምጃ እንደተወሰደባቸው የመተማ ወረዳ ሰላምና ደህንነት ጽ/ቤት አስታወቀ።

የወረዳው ሰላምና ደህንነት ፅ/ቤት ፥ " የማህበረሰብ እንቅስቃሴ ሲያውኩ የነበሩ ሶስት ጸረ-ሰላም ኃይሎች በጥምር የጸጥታ ኃይል (ልዩ ኃይል ፣ ፀረሽምቅ እና ፖሊስ) ርምጃ ተወስዶባቸዋል " ብሏል።

በጣምራ ስምሪቱ ርምጃ የተወሰደባቸው የማህበረሰብ እንቅስቃሴ ሲያውኩ የነበሩ ሰው በማገት ፣ ሰው በመግደል ሲፈለጉ የነበሩ 3 ግለሰቦች መሆናቸውን ፅ/ቤቱ አሳውቋል።

ርምጃ የተወሰደባቸው ፦ 1. ፎላ አብተው - አድራሻ መተማ ወረዳ ጉባይ ጀጀቢት ቀበሌ ፤ 2. ደሴ አበራ - መተማ ወረዳ ጉባይ ጀጀቢት ቀበሌ ፤ 3. ሱራፌል ወርቁ - ከደጋ አካባቢ የመጣ መሆኑን ፅ/ቤቱ ይፋ አድርጓል።

በስምሪቱ 1 ቋም ክላሽ ፣ 2 ኤም 14 ፣ 1 ስናይፐር የተማረከ መሆኑን ጽ/ቤቱ ገልጿል።

@tikvahethiopia
#ጥንቃቄ

የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ባለፉት ጥቂት ቀናት ከወትሮው የተለየ ከፍተኛ የሆነ የሙቀት መጠን እንየተስተዋለ መሆኑን ጠቁሟል።

ይህን አስመልክቶም የአስተዳደሩ ጤና ቢሮ ለነዋሪዎችም የጥንቃቄ መልዕክት አስተላልፏል።

በተለይም ፦ አረጋውያን እና የተለያዩ ተጓዳኝ ህመም ያለባቸው (ከፍተኛ ደም ግፊት፣የስኳር ህመም፣ የልብ ህመም፣ የኩላሊት ህመምና ሌሎችም)፣ እራሳቸውን መንከባከብ የማይችሉ የአይምሮ ህሙማን እና ህፃናት በተለየ መልኩ የጥንቃቄ መልእክቶች ተግባራዊ እንዲያደርጉ ቢሮው አሳስቧል።

ሊደረጉ የሚገባቸው የጥንቃቄ ተግባራት ፦

1. ወቅታዊው ከፍተኛ የሙቀት መጠን እስኪያልፍ መኖሪያ ቤትዎን በተለያዩ መንገዶች ማቀዝቀዝ፣

2. እቤትዎ በሚሆኑበት ግዜና በእንቅልፍ ወቅት የቤትዎን መስኮትና በር ክፍት ማድረግ፣

3. በቤትዎ የአየር መታፈን እና ከፍተኛ ሙቀት በሚኖርበት ወቅት ከቤትዎ ውጪ/በረንዳዎ ላይ መቆየት፣

4. ጥም ባይኖርቦትም በቂ ፈሳሽ/ውሃ/ መውሰድ፣

5. አመጋገብዎን ማስተካከል (ስብና ቅባት የበዛባቸው ምግቦችን መቀነስ)፣

6. ቀለል ይሉ አካላዊ እንቅስቃሴዎችን ጥላማ በሆኑ ቦታዎች ላይ መስራት፣

7. የአልኮል መጠጦችን አለመጠቀም/መቀነስ፣

8. ህፃናትን እና የአዕምሮ ህሙማንን በተዘጉ/አየር በሌላቸው ክፍሎች ለብቻ አለመተው፣

9. የተለያየ ህመም ማለትም እንደ ከፍተኛ ደም ግፊት፣ ስኳርና የልብ ህመም ካለብዎ የህክምና ክትትልዎን በሚገባ ያድርጉ ፡ የታዘዘሎትን መድሃኒትም በትዕዛዙ መሰረት ይውሰዱ።

የድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ ፤ ከሙቀቱ ጋር ተያይዘው ከሚከሰቱ የጤና ችግሮችና ድንገተኛ ህልፈት ነዋሪዎች ራሳቸውንና ቤተሰባቸውን እንዲጠብቁ የጥንቃቄ መልዕክት አስተላልፏል።

@tikvahethiopia