TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
ዲቪ (DV) 2023 ይፋ ሆኗል። የ2023 ዲቪ ሎተሪ ዛሬ ማታ ይፋ የሆነ ሲሆን ሞልታችሁ ስትጠባበቁ የነበራችሁ በሙሉ የዲቪ ውጤታችሁን በዚህ ሊንክ https://dvprogram.state.gov/ESC/Default.aspx መመልከት ትችላላችሁ ተብሏል። @tikvahethiopia
#ዲቪ_ሎተሪ

ዳይቨርሲቲ ቪዛ ሎተሪ (ዲቪ) አሜሪካ በዕጣ የምትሰጠው የቪዛ መርሀ ግብር ሲሆን ከተወሰኑ ሀገራት በስተቀር ከመላው ዓለም በየዓመቱ ከ50 ሺህ በላይ ፍልሰተኖች አሜሪካ ገብተው የመኖር እና የመስራት ፍቃድ ያገኛሉ።

የአሜሪካ መንግስት ከዐለም የተለያዩ ሀገራት ዜጎችን የዲቪ ሎተሪን እየተጠቀሙ ወደ ግዛቱ እንዲገቡ ማድረግ ከጀመር በርካታ አመታት ተቆጥረዋል።

ለተሻለ ኑሮና ጥሩ የሆነ ግቢ አግኝቶ ሰርቶ ቤተሰብን ለመቀየረ የዲቪ ሎተሪ የሚያመለክቱ በየዓመቱ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎች ናቸው።

አሜሪካ ከተወሰኑ ሀገራት በቀር በመላው ዓለም ላሉ ሀገራት በምታመቻቸው ከ50 ሺህ በላይ የቪዛ ዕድል አንድ ሀገር የሚደርሰው ከሰባት በመቶ የማይበልጥ ነው።

ከሀገራችን ኢትዮጵያ ለዚህ ዕድል የሚያመለክቱ እጅግ በርካቶች ናቸው።

ለዲቪ የሚያመለክቱ አንድም በትምህርት አልያም በስራ ልምድ የሚወጡ መስፍርቶችን እንዲያሟሉ የሚጠበቅ ሲሆን በትምህርት ደረጃ ቢያንስ የ2ኛ ደረጃን ማጠናቀቅ አለባቸው፤ የኮሌጅና የዩኒቨርሲቲ ምሩቃን ቢሆኑ ደግሞ ጥሩ ነው፤ የትምህርት መመዘኛውን የማያሟሉ በስራ ልምድ ማካካስ የሚችሉ ሲሆን የስራ ልምድ ማስረጃ መያዝ አለባቸው።

በየዓመቱ የዲቪ ሎተሪ ሲሞላ አልያም ሲወጣ የማጭበርበር ድርጊቶች በስፋት ይስተዋላል፤ አጭበርባሪዎች ሰዎችን " የዲቪ እድል ደርሷችኃል " በማለት ያጭበረብራሉ፤ ማንኛውም ሰው ለዲቪ ሲያመለክት ሆነ ውጤት በሚታያይበት ወቅት የአሜሪካ መንግስት ለዚህ ክትትል አንዳች ክፍያ አያስከፍልም።

የ " 2023 የዲቪ ሎተሪ ዕጣ " ትላንት ምሽት ይፋ የተደረገ ሲሆን በዚህ ሊምክ መመልከት ይቻላል : https://dvprogram.state.gov/ESC/Default.aspx

@tikvahethiopia
#iጤና

• በስትሮክ፣ በአደጋ፣ እና በሌሎች በሽታዎች ምክንያት ሙሉ ለሙሉ ወይም በከፊል ለተፈጠረ አለመንቀሳቀስ (Paralysis)
• እድሜ በመግፋት ለሚፈጠሩ ጉድለቶች እንደ አልዛይመርስ፤ ዲሜንሻ
• ከተለያዩ ቀዶ ጥገናዎች ለማገገም
• በሙሉ (Coma) ወይም በከፊል የንቃተ ህሊና መቀነስ ላላቸው ታካሚዎች እንክብካቤ
• ለካንሰር እና ተከታታይ የህክምና ክትትል ለሚያስፈልጋቸው ታካሚዎች

👉 በ0901222233 ይደውሉልን
Telegram | FB | IG | Twitter 🌍
🏥 አድራሻችን ጀሞ ከ ጀሞ ሞል 200m ገባ ብሎ፡፡
በሀገራችን በተለይ በአዲስ አበባ እጅግ በጣም ሙስና ስር ከሰደደበት አንዱ የመሬት ዝውውር ጉዳይ ነው።

በዚህ ሂደት አንዳንድ የአስተዳደሩ አመራሮችና ባለሙያዎች ደላላ ሆነው የተገኙበት ጊዜ መኖሩ ተጠቁሟል።

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ አስተዳደር የፐብሊክ ሰርቪስና ሰው ሃብት ልማት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሂክማ ከይረዲን ለኢፕድ በሰጡት ቃል ፥ " " በመሬት ጉዳይ ብልሹ አሰራሮች በከተማው ተስፋፍቷል፣ በተለይ ደላላ የበዛበትና ለሙስና የተጋለጠ የመሬት ዝውውር ስርዓት በከተማዋ ታይቷል " ብለዋል።

አክለው፥ አንዳንድ የከተማ አስተዳደሩ አመራሮችና ባለሙያዎች #ከባለሃብት_ጋር_በመመሳጠር መሬትን በህገወጥ መንገድ ለማስተላለፍ የሚደረጉ ሙከራዎች በተደጋጋሚ መታየታቸውን ተናግረዋል።

ወ/ሮ ሂክማ ፤ በመረጃ በተደገፈ ሁኔታ የተያዙ አመራሮችና ባለሙያዎች ወደሕግ እንዲቀርቡ መደረጉንም ለኢፕድ ጋዜጣ ገልጸዋል።

እነዚህ ተይዘው ወደህግ ቀረቡ የተባሉ አመራሮች እና ባለሞያዎች እነማን እንደሆኑ በምን አይነት የኃላፊነት ቦታ እንደነበሩ በግልፅ ዘገባው ላይ የተብራራ ነገር የለም።

የከተማው አስተዳደር ፤ የመሬት አገልግሎትን በተመለከተ በቀጣይነት ሁለት አይነት አሰራር እንደሚተገበር የተጠቆመ ሲሆን ፥ መሬትን ዲጂታላይዝ በማድረግ የግልጸኝነት አሰራርን ማስፈን እና የመረጃ አያያዝ ሥርዓቱን በማጠናከር ሕዝብ እያንዳንዱን መረጃ እንዲያገኝ ማድረግ የትግበራው አካል መሆኑንም ነው የተገለፀው።

መሬት ለሌላ አካል የሚተላለፍበት መንገድ ህዝብን እንዲያሳትፍ አቅጣጫ መቀመጡንም ተነግሯል።

ያንብቡ : https://telegra.ph/EPA-05-09

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
በሀገራችን በተለይ በአዲስ አበባ እጅግ በጣም ሙስና ስር ከሰደደበት አንዱ የመሬት ዝውውር ጉዳይ ነው። በዚህ ሂደት አንዳንድ የአስተዳደሩ አመራሮችና ባለሙያዎች ደላላ ሆነው የተገኙበት ጊዜ መኖሩ ተጠቁሟል። በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ አስተዳደር የፐብሊክ ሰርቪስና ሰው ሃብት ልማት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሂክማ ከይረዲን ለኢፕድ በሰጡት ቃል ፥ " " በመሬት ጉዳይ…
#AddisAbaba

በአዲስ አበባ ከተማ ከመሬት አገልግሎት ጋር በተያያዘ ወ/ሮ ሂክማ ከይረዲን ከተናግሩት ፦

" ... በአዲስ አበባ ከተማ በእጅ መንሻ፣ በዝምድናና በተለያዩ ህገወጥ አካሄዶች ጉዳዮቻቸው #በፍጥነት የሚፈጸምላቸው ሰዎች አሉ። በአንጻሩ ደግሞ ህግን ተከትሎ የሚመጣው ደንበኛ ሲንገላታ ይስተዋላል። ችግሩ በተለይ በክ/ከተሞችና ወረዳዎች ላይ ሰፊውን ህዝብ ለእንግልት እየዳረገው ነው። በመሆኑም ከተማ አስተዳደሩ አፋጣኝ ማስተካከያዎችን እየወሰደ ይገኛል። "

#EPA

@tikvahethiopia
APS-Call-for-Applications_FY2022-final-1.pdf
280.5 KB
#ጥቆማ

በአዲስ አበባ የአሜሪካ ኤምባሲ በፐብሊክ ዲፕሎማሲ በኩል የገንዘብ ድጋፍ እድሎች መኖራቸውን ጠቁሟል።

ማንኛውም ሰው በአሜሪካና ኢትዮጵያ መካከል ያለውን " የባህል ግንኙነት የሚያጠናክር " ፕሮፖዛል የጋራ እሴቶችን በሚያጎላ እና የሁለትዮሽ ትብብርን በሚያበረታታ የባህል ወይም የሚዲያ ልውውጥ በኩል ማቅረብ ይችላል።

👉 Funding Opportunity Title : U.S. Embassy Addis Ababa PAS Annual Program Statement

👉 Funding Opportunity Number : PAS-APS-FY22

👉 CFDA Number : 19.040-Public Diplomacy Programs

👉 Date Opened: March 21, 2022

👉 Deadline for Applications: June 01, 2022

👉 Maximum for Each Award :$200.000

👉 Federal Agency Email: PASAddisGrants@state.gov

ከላይ በPDF በተያያዘው ፋይል መመሪያዎችን በጥንቃቄ አንብበው ይከተሉ ፤ የመጨረሻው የፕሮፖዛል የማስረከቢያ ቀን እ.ኤ.አ. ሰኔ 18፣ 2022 ነው።

@tikvahethiopia
#አብን

የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ ከድርጅት ህገ-ደንብ እና አሰራር ውጭ በመሆን አፍራሽ ድርጊቶችንና የዲሲፕሊን ጥሰቶችን ፈፅመዋል ባላቸው ከፍተኛ እና መካከለኛ አመራሮች ላይ የእርምት ውሳኔ ማሳለፉን አሳውቋል።

የፓርቲው ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ በ29/8/2014 ዓ.ም ባደረገው አስቸኳይ ስብሰባ ነው በፓርቲው መዋቅር የተለያዩ የሃላፊነት እርከኖች ውስጥ እየተከሰቱ ያሉ የዲሲፕሊን እና ድርጅታዊ መርህ ጥሰቶችን በተመለከተ ተወያይቶ የድርጅቱን መተዳደሪያ ደንብ የተለያዩ ድንጋጌዎችን መሰረት በማድረግ ውሳኔዎችን ማሳለፉን ያሳወቀው።

ፓርቲው በዚህ ውሳኔው የንቅናቄው የስራ አስፈጻሚ አባል አቶ ክርስቲያን ታደለን የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ የሰጣቸው ሲሆን " የንቅናቄው ከፍተኛ አመራር ሆነው ሳለ ፣ የተጣለባቸውን ከፍተኛ ሃላፊነት ወደ ጎን በመተው በተለያዩ አፍራሽ ድርጊቶች ላይ የተሳተፉ ሲሆን ፣ ከዚህ ቀደም ከድርጊታቸው እንዲታቀቡ ሁለት ጊዜ የቃል ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷቸዋል " ሲል ገልጿል።

" ይሁን እንጂ አሁንም በንቅናቄው ሥራ አስፈፃሚነታቸውም ሆነ በማዕከላዊ ኮሚቴ አባልነታቸው በጋራ ለሚወሰኑ ውሳኔዎች ተገዥ ባለመሆን እና ንቅናቄውን ለማፍረስ ከሚንቀሳቀሱ አንጃኞች ጋር ሕብረት በመፍጠርና ፣ ንቅናቄው የሃሳብና የተግባር አንድነት እንዳይኖረው በሚያደርጉ ተግባራት ላይ ተሰማርተው ስተለገኙ የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ እንዲሰጣቸው ተወስኗል " ብሏል።

በሌላ በኩል ፤ ፓርቲው 10 የመካከለኛ አመራሮች እና አባላትን ከድርጅቱ ያገደ ሲሆን ለሁለት የቋሚ ኮሚቴዎች አባላት ጥብቅ ማስጠንቀቂያ ሰጥቷል።

(ተጨማሪ ዝርዝር መረጃ ከላይ በደብዳቤው ተያይዟል)

@tikvahethiopia
#የመኪና_መገልበጥ_አደጋ

ከወረኢሉ ከተማ ወደ አዲስ አበባ ሲጓዝ የነበረ የሰሌዳ ቁጥሩ " ኮድ 3 ኢት 76088 " የሆነ የህዝብ ማመላለሺያ አውቶቢስ ተጓዦችን ጭኖ ሲጓዝ ግንቦት 1/2014 ዓ/ም ከጧቱ 2 ሰአት አካባቢ በሰ/ሸዋ ዞን ሚዳ ወረሞ ወረዳ ወርቄ ቀበሌ ልዩ ስሙ ጨለሚት ከሚባለው ቦታ የመገልበጥ አደጋ ደርሶበታል።

በደረሰው አደጋ እስካሁን 8 ከባድ የአካል ጉዳት ደርሶ ለከፍተኛ ህክምና ሪፈር የተባሉ ሲሆን ከ40 ሰው በላይ ቀላል አደጋ ደርሶ በሚዳ ወረሞ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፓታል በህክምና ላይ ናቸው።

የአደጋው መንስኤ ፖሊስ በማጣራት ላይ መሆኑን የሚዳ ወረሞ ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት መግለፁን ከወረዳው ኮሚኒኬሽን የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

@tikvahethiopia
" ምዕራባውያን ለሩሲያ ስጋት ሆነው ቀጥለዋል " - ፕሬዜዳንት ቭላድሚር ፑቲን

እኤአ ሜይ 9 ሩሲያውያን በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ማብቂያ ላይ ሶቪዬት ሕብረት በናዚ ጀርመን ላይ የተቀዳጀችውን ድል አስበው ይውላሉ።

ይህ የድል በዓል ቭላድሚር ፑቲን ወደ ስልጣን ከመጡ በኋላ ትልቅ ትርጉም ተሰጥቶት ነው የሚከበረው።

በዕለቱ ሩሲያ ያላትን ዘመን አፈራሽ ጦር መሳሪያ ለዓለም የምታሳይበት ቀን አድርገውታል።

ከዩክሬን ጋር ጦርነት ላይ ያሉት የሩስያው መሪ የዛሬውን የድል ቀን ምክንያት በማድረግ ከዩክሬን ጋር እየተደረገ ያለውን ጦርነቱ የተመለከተ አዲስ ውሳኔ ያስተላልፋሉ ተብሎ ተጠብቆ ነበር።

ፑቲን በዛሬው በዓል ላይ ጦርነቱ ማብቃቱን አልያም በዩክሬን ላይ አዲስ የተጠናከረ ወታደራዊ እርምጃ ይወሰዳል ብለው ይናገራሉ ተብሎ ሲጠበቅ ነበር።

ነገር ግን " ምዕራባውያን ለሩሲያ ስጋት ሆነው ቀጥለዋል " ከማለት ውጪ ፑቲን ያሉት ነገር የለም።

ፑቲን በዩክሬን እየተፋለሙ ላሉት ወታደሮቻቸው "እየተዋጋችሁ ያላችሁት ለሩስያ ደኅንነት ነው” በማለት መልዕክት አስተላልፈዋል።

Via BBC NEWS

@tikvahethiopia
#አቢሲንያ_ባንክ

በአቢሲንያ ኢ-ኮሜርስ የክፍያ አማራጭ የቪዛ እና ማስተር ካርድዎን በመጠቀም ከየትኛውም የዓለም ክፍል ለሆቴል ፣ ለግብይት ፣ ለጉብኝት ክፍያ ይፈጽሙ፣ ለወዳጅ ዘመድዎ አስቤዛ ያድርጉ ፣ እንዲሁም የተለያዩ አገልግሎቶችን በቀላሉ ያግኙ! የሁሉም_ምርጫ !

የአቢሲንያ ባንክን ትክክለኛ የቴሌግራም ቻናል ይቀላቀሉ! https://publielectoral.lat/BoAEth
TIKVAH-ETHIOPIA
#አብን የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ ከድርጅት ህገ-ደንብ እና አሰራር ውጭ በመሆን አፍራሽ ድርጊቶችንና የዲሲፕሊን ጥሰቶችን ፈፅመዋል ባላቸው ከፍተኛ እና መካከለኛ አመራሮች ላይ የእርምት ውሳኔ ማሳለፉን አሳውቋል። የፓርቲው ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ በ29/8/2014 ዓ.ም ባደረገው አስቸኳይ ስብሰባ ነው በፓርቲው መዋቅር የተለያዩ የሃላፊነት እርከኖች ውስጥ እየተከሰቱ ያሉ የዲሲፕሊን እና ድርጅታዊ መርህ ጥሰቶችን…
" ...መሰል ውሳኔዎችን ለመወሰን የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴው ሥልጣን የለውም " - አቶ ክርስቲያን ታደለ

የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ ከድርጅት ህገደንብ እና አሰራር ውጭ በመሆን አፍራሽ ድርጊቶችን እና የዲሲፕሊን ጥሰቶችን ፈፅመዋል ባላቸው ከፍተኛ እና መካከለኛ አመራሮች ላይ የእርምት ውሳኔ ማስለፉ ይታወቃል።

ፓርቲው ይህን የእርምት ውሳኔ ማሳለፉን የሚገልፅ ደብዳቤም በይፋዊ የማህበራዊ ትስስር ገፁ ላይ አሰራጭቷል።

ውሳኔ ከተላለፈባቸው አመራሮች አንዱ የንቅናቄው ስራ አስፈፃሚ አባል አቶ ክርስቲያን ታደለ ሲሆኑ ፓርቲው " የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ " እንዲሰጣቸው ውሳኔ አሳልፏል አቶ ክርስቲያን ይህን የተላለፈውን ውሳኔ በተመለከተ በተረጋገጠ የማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ላይ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።

አቶ ክርስቲያን ፤ " በአብን የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ስም የወጣውን መግለጫ ያየሁት ዘግይቼ ነው " ያሉ ሲሆን " ፍሬ ነገሩ ልክ ይሁንም፥ አይሁንም መሰል ውሳኔዎችን ለመወሰን ግን የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴው ሥልጣን የሌለው መሆኑን ለንቅናቄያችን አባላትና ደጋፊዎች መግለጽ እፈልጋለሁ " ብለዋል።

አክለውም " ንቅናቄው የተመሰረተባቸውን ሕዝባዊና አገራዊ ጥያቄዎች ከግብ እንዲያደርስ ሁላችንም በጎ ሚና እንድንጫዎት አደራ ማለት እፈልጋለሁ " ሲሉ ገልፀዋል።

አብን በማህበራዊ ትስስር ገፁ ዛሬ ይፋ ባደረገው የእርምት ውሳኔ ለአቶ ክርስቲያን ታደለ የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ ከመስጠት ባለፈ 10 የመካከለኛ አመራሮች እና አባላትን ከድርጅቱ አግዷል፤ ለሁለት የቋሚ ኮሚቴዎች አባላት ደግሞ ጥብቅ ማስጠንቀቂያ ሰጥቷል።

@tikvahethiopia