TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ አርፈዋል። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አራተኛው ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል። የቅዱስነታቸውን ሽኝት በተመለከተ ቅዱስ ሲኖዶስ ዛሬ ተሰብስቦ በሚያስተላልፈው ውሳኔና በሚያወጣው መርሐ ግብር መሰረት የሚፈጸም መሆኑን የኢኦተቤ ህዝብ ግንኙነት አሳውቋል። አራተኛው የኢትዮጵያ ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ…
#Update

ቅዱስ ሲኖዶስ ባካሄደው አስቸኳይ ጉባኤ የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ሥርዓተ ቀብር እሑድ እንዲፈጸም ወስኗል።

የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ 4ኛው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ አቡነ መርቆሬዎስ ሥርዓተ ቀብር እሑድ ዕለት እንዲፈጸም ውሳኔ አሳልፏል፡፡

የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ሥርዓተ ቀብር በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል እንደሚከናወን ተገልጿል።

@tikvahethiopia
Situation_Report_Northern_Ethiopia_Humanitarian_Update_3_Mar_2022.pdf
3.1 MB
#UNOCHA

PDF የሰሜን ኢትዮጵያ ወቅታዊ የሰብዓዊ ድጋፍ ሁኔታ ሪፖርት።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Situation_Report_Northern_Ethiopia_Humanitarian_Update_3_Mar_2022.pdf
#SituationReport

#Tigray #Amhara #Afar📍

የሰሜን ኢትዮጵያ ያለው ወቅታዊ ሁኔታ በተመለከተ የተመድ ሰብዓዊ እርዳታ ማስተባበሪያ የዚህን ሳምንት ሪፖርቱን ይፋ አድርጓል።

ዋና ዋና ነጥቦች ፦

#Afar📍

- በአፋር ክልል በአንዳንድ አካባቢዎች ያለው ሁኔታ ተባብሶ ቀጥሏል። በተለይም በራህሌ፣ ኢሬብቲ፣ ኬልቤቲ ዞን (ዞን 2) ውስጥ የትጥቅ ግጭቶች መኖራቸው ሪፖርት ተደርጓል።

- በአፋር እየተካሄደ ያለው ግጭት የሰብአዊ ድጋፍ መርሃ ግብሮችን እያደናቀፈ ፤ የሲቪሎችን ህይወት፣ ደህንነታቸውን አደጋ ላይ እየጣለ እና ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ የሚሄደው የተፈናቀሉ ሰዎች ቁጥርም የሰብአዊ ፍላጎቶችን እየጨመረው ይገኛል።

- በአፋር ክልል ዞን 4 መረጋጋት በመፈጠሩ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ የውስጥ ተፈናቃዮች ወደ ቀደመው ቀያቸው ተመልሰዋል።

- በዞን 2 በቀጠለው ግጭት ምክንያት ተጨማሪ በመቶ ሺህ የሚቆጠሩ ሰዎች ከመኖሪያ ቀያቸው መፈናቀላቸውን የክልሉ ባለስልጣናት አሳውቀዋል። ተፈናቃዮቹ በተለይም ከአባላ፣ ኢረብቲ፣ በረሃሌ፣ መጋሌ እና ዳሎል ወረዳዎች መሆናቸው ተገልጿል። አብዛኞቹ ተፈናቃዮች በአሁኑ ወቅት በዳሎል፣ አፍዴራ፣ ሲልሳ/ጉያህ እና ሰመራ እየተጠለሉ ሲሆን አንዳንድ ተፈናቃዮች ደግሞ ራቅ ባሉ እና ለመድረስ አስቸጋሪ በሆኑ አካባቢዎች ነው ያሉት።

- የተመድ አጋሮች በተደራሽነት ውስንነት ምክንያት በዞን 2 የሚገኙትን የተፈናቃዮች ቁጥር ማረጋገጥ አልቻሉም።

- ቁጥራቸው ያልተረጋገጠ ከአፋር የተፈናቀሉ ተፈናቃዮች በትግራይ ክልል በሚገኙ ጥቂት ትምህርት ቤቶች ይገኛሉ።

#Tigray 📍

- አሁን ላይ የ ሰመራ - አብአላ - መቐለ መስመር መዘጋት ወደ ትግራይ የሚደርሰውን የሰብአዊ አቅርቦት የበለጠ አባብሶታል። ሰብዓዊ አቅርቦቱ ከታህሳስ አጋማሽ በፊት ከተፈቀደው ውስን አቅርቦት ጋር ተዳምሮ በዋነኛነት ቀደም ባሉት አስተዳደራዊ ርምጃዎች ምክንያት ሰብዓዊ አቅርቦቱ ከሚያስፈልገው በታች ነበር።

- እኤአ ከሃምሌ 12 ጀምሮ አስፈላጊውን የሰብአዊ አቅርቦት ከያዙ 16,500 የጭነት መኪናዎች ውስጥ 8 በመቶው ብቻ ትግራይ ገብተዋል። በዚህም የተመድ ሰብአዊ አጋሮች ተግባራቸውን መቀነሳቸውን ቀጥለዋል።

- ይህ ሪፖርት በተዘጋጀበት በዚህ ሳምንት የሰብአዊ ድጋፍ አድራጊ ድርጅቶች 47 ሜትሪክ ቶን የህክምናና የስነ ምግብ አቅርቦቶችን ወደ ትግራይ ክልል መዲና መቐለ በበረራ አድርሰዋል። ይህ እኤአ ከጥር 24 አንስቶ በበረራ ወደ ትግራይ የገባውን አጠቃላይ አቅርቦት 144 ሜትሪክ ቶን አድርሶታል።

- በዚህ ሳምንት ወደ ትግራይ ከቀረበው አቅርቦት መካከል 10 ሜትሪክ ቶን የተመጣጠነ ምግብ (Ready to Use Therapeutic Food - RUTF) ይገኝበታል። ይህም ከታህሳስ አጋማሽ ጀምሮ ለመጀመሪያ ጊዜ የገባ ሲሆን በመቐለ፣ በምስራቅ እና ደቡብ-ምስራቃዊ ዞን ይከፋፈላል። ከፍተኛ የሆነ የተመጣጠነ ምግብ እጥረት ያለባቸው ከ5 ዓመት በታች የሆኑ ህጻናትን ለመንከባከብ ይውላል።

- ባለፉት ሳምንታት ወደ መቐለ የደረሱ የህክምና ቁሳቁሶች ይህ ሪፖርት በተዘጋጀበት ሳምንት ወደ ምስራቅ ዞን ውቅሮ እና ዓዲግራት አጠቃላይ ሆስፒታሎች፣ ወደ ማዕከላይ ዞን ዓድዋ፣ አክሱም፣ አቢአዲ ጠቅላላ ሆስፒታሎች እና አክሱም ሪፈራል ሆስፒታል፣ በሰሜን ምዕራብ ዞን ወደ ስሁል ሽሬ አጠቃላይ ሆስፒታል ተከፋፍለዋል።

- አሁንም የነዳጅ እጥረት ቀሪዎቹን ቁሳቁሶች ለማከፋፈል እንቅፋት እንደሆነ ነው።

- በትግራይ አሁንም የህክምና ቁሳቁሶች ችግርና የተወሰኑ አይነት መድሃኒት እጥረቶች ያሉ ሲሆን ከነዚህም መካከል HIV ላለባቸው ሰዎች ሚሰጥ መድሃኒት ይጠቀሳል፣ የHIV መመርመሪያ ኪት፣ የፀረ ራቢስ መድሃኒት፣ የኮሌራ ክትባት እጥረትም አለ።

#Amhara 📍

- በአማራ ክልል አንዳንድ ' ከትግራይ አዋሳኝ አካባቢዎች ' አሁንም ተደራሽ አይደሉም። በተለይም በሰሜን ጎንደር ፣ ዋግ ኽምራ እና ሰሜን ወሎ ዞኖች ያሉ አካባቢዎች እጅግ አሳሳቢ ሲሆኑ አልፎ አልፎ በሚከሰቱት ግጭቶች ምክንያት ሰዎች ወደ ዝቋላ ፣ ሰቆጣ ፣ ቆቦ እና ዛሪማ መፈናቀላቸውን የሚገልፁ ሪፖርቶች አሉ።

- በሰቆጣ እና ዝቋላ ከ40 ሺ በላይ ተፈናቃዮች እንደሚኖሩ ይገመታል።

- በአማራ ክልል በዘጠኝ ዞኖች እኤአ ከታህሳስ እስከ ጥር ባለው ጊዜ ውስጥ በ " Find -and - Treat " ዘመቻ ከ1 ነጥብ 9 ሚሊየን በላይ ህጻናትን የመለየት ዘመቻ የተካሄደ ሲሆን ከእነዚህም ውስጥ 21,804 ህጻናት ወይም 1.1 በመቶው ህጻናት በከፋ የምግብ እጥረት (SAM) ተጠቅተዋል።

- በምስራቅ አማራ እ.ኤ.አ. ከየካቲት 14 ጀምሮ በመካሄድ ላይ ባለው 'find and treat' ዘመቻ እስካሁን ምርመራ ከተደረገላቸው 293,208 ከ5 አመት በታች ህጻናት 8,160 SAM ኬዝ ወይም 2.7 በመቶና 48,118 GAM ኬዞች ወይም 16.4 በመቶ ተገኝቷል። ምርመራ ከተደረገላቸው 52,828 ነፍሰጡር እና የሚያጠቡ እናቶች ውስጥ 21,687 ሴቶች ወይም 41 በመቶው የተመጣጠነ ምግብ እጥረት አለባቸው ተብሏል።

#UNOCHA

@tikvahethiopia
#ETHIOPIA #UKRAINE #RUSSIA

ሩስያ ዩክሬን ላይ የጀመረችው ወታደራዊ ዘመቻ ተከትሎ በኢትዮጵያ ላይ የሚፈጠር ጫና እንደሚኖር የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር እዮብ ተካልኝ ተናግረዋል።

ዶ/ር እዮብ ለፋና ብሮድካስት በሰጡት ቃል ፤ " ሩስያ እና ዩክሬን የንግድ አጋሮቻችን እንደመሆናቸው የሚፈጠር ጫና ይኖራል " ብለዋል።

" ያም ሆኖ ግን ከሀገራቱ በብዛት ኢትዮጵያ ምታስገባው ስንዴ ለዚህ ዓመት የሚበቃው ቀድሞ በመገዛቱ ተፅእኖው ፈጥኖ ላይደርስብን ይችላል " ሲሉ ሚኒስትር ዴኤታው አስረድተዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ አርፈዋል። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አራተኛው ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል። የቅዱስነታቸውን ሽኝት በተመለከተ ቅዱስ ሲኖዶስ ዛሬ ተሰብስቦ በሚያስተላልፈው ውሳኔና በሚያወጣው መርሐ ግብር መሰረት የሚፈጸም መሆኑን የኢኦተቤ ህዝብ ግንኙነት አሳውቋል። አራተኛው የኢትዮጵያ ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ…
#USA

አሜሪካ በብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ አቡነ መርቆሬዎስ እረፍት የተሰማትን ሀዘን ገለፀች።

አሜሪካ 🇺🇸 በአዲስ አበባ ባለው ኤምባሲዋ አማካኝነት በ4ኛው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ አቡነ መርቆሬዎስ እረፍት የተሰማትን ሀዘን ገልፃለች።

ሀገሪቱ በሀዘን ላይ ላሉ ሁሉ መፅናናትን ተመኝታለች።

@tikvahethiopia
#Russia

የሩስያ የኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ተቆጣጣሪ ቡድን የዩክሬን ግጭትን አስመልክቶ ሀሰተኛ መረጃዎችን እያሰራጩ ነው ባላቸው የብሪቲሽ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (#ቢቢሲ) እና የራዲዮ ሊብሪቲ ድረ-ገጾች ላይ ገደብ ጥሏል።

ሩስያ የምዕራባውያን ሚዲያዎች ፤ በውጭ ሀገራት ጦርነት ለምሳሌ እንደ #ኢራቅ ባሉ እና በሙስና እጃቸው ያለባቸው የገዛ የራሳቸው ሀገራት መሪዎች ተጠያቂ ማድረግ ሳይችሉ በከፊል እና ብዙ ጊዜ ፀረ-ሩሲያ የሆነ አመለካከትን ለዓለም ያስተላልፋሉ ስትል በተደጋጋሚ ስትወቅስ ቆይታለች።

ከዩክሬን ጋር በተያያዘ የሩስያ ባለስልጣናት "ወረራ" ሚለውን ቃል የማይጠቀሙ ሲሆን የምዕራባውያን ሚዲያዎች ዩክሬን ውስጥ በሩሲያኛ ተናጋሪ ህዝቦች ላይ የሚፈፀመውን " የዘር ማጥፋት ወንጀል " ሪፖርት እንደማያደርጉ ይናገራሉ።

ሩስያ ምዕራባውያን ሚዲያዎች ላይ ገደብ ከመጣሏ በፊት ምዕራባውያኑም በሩስያ ሚዲያዎች ላይ የተለያዩ ገደቦችን ጥለዋል።

ለአብነት ዩናይትድ ኪንግደም በሩስያ የሚደገፈው " ራሺያ ቱዴይ " ቴሌቪዥን ዩናይትድ ኪንግደም ውስጥ እንዳይታይ አግዳዋለች።

@tikvahethiopia
" እንቅጠራችሁ እና ዩክሬን ሄዳችሁ ከሩስያ ጋር ተዋጉልን " - የዩክሬን ኤምባሲ

ሴኔጋል ዳካር ከተማ ሚገኘው የዩክሬን ኢምባሲ በጎ ፈቃደኛ ሴኔጋላዊያን እና ሌሎችም የውጭ ሀገራት ዜጎች ወደ ዩክሬን አምርተው ከሩሲያ ጋር እየተደረገ ባለው ጦርነት እንዲዋጉ የቅጥር ማስታወቂያ አውጥቷል።

ይህ ማስታወቂያ ሴኔጋልን አበሳጭቷል።

የሴኔጋል ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በዳካር የዩክሬን አምባሳደር ዩሪ ፒቮቫሮቭ በጉዳዩ ዙሪያ ማብራሪያ እንዲሰጡ ጠርቷል።

ሚኒስቴሩ የኢምባሲው ድርጊት የሀገራት የዲፕሎማሲ ግንኙነት ዙሪያ የወጣው የቬና ድንጋጌዎችን የሚጥስ ነው ብሏል።

ኤምባሲው ወደ ዩክሬን ሄደው እንዲዋጉ ያወጣወን የቅጥር ማስታወቂያ ቆይቶ ያጠፋ ቢሆንም በቀጣይ ምን አይነት እርምጃዎችን ሊወስድ እንደሚችል ግልጽ አይደለም በሚል የሴኔጋል ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መግለፁን አል ዓይን ኒውስ ዘግቧል።

ሴኔጋል በተመድ ጠቅላላ ጉባኤ (UNGA) ላይ የቀረበውን " ሩስያ ዩክሬንን ወራለች ፤ ወታደሮቿንም ከዩክሬን ታስወጣ " የሚለውን የውሳኔ ሃሳብ ላይ የድምጸ ተዓቅቦ ካደረጉ ሀገራት አንዷ ናት።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ አርፈዋል። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አራተኛው ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል። የቅዱስነታቸውን ሽኝት በተመለከተ ቅዱስ ሲኖዶስ ዛሬ ተሰብስቦ በሚያስተላልፈው ውሳኔና በሚያወጣው መርሐ ግብር መሰረት የሚፈጸም መሆኑን የኢኦተቤ ህዝብ ግንኙነት አሳውቋል። አራተኛው የኢትዮጵያ ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ…
#Russia

ሩስያ በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ እረፍት የተሰማትን ሀዘን ገለፀች።

ሩስያ በአዲስ አበባ ባለው ኤምባሲዋ አማካኝነት በ4ኛው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ አቡነ መርቆሬዎስ እረፍት የተሰማትን ሀዘን ገልፃለች።

የብጹዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ እረፍት በዓለም ለሚገኙ የኦርቶዶክስ አማኞች ከባድ ሐዘን ነው ብላለች።

ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ-ክርስቲያን ታላቅነት ማስቀጠልና መጠበቅ ውስጥ የማይተካ ሚና መጫወታቸውንም ሩስያ ገልፃለች።

ሩስያ በብፁዕነታቸው እረፍት ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጋር ሆነን እናዝናለን ብላለች።

@tikvahethiopia
#NEBE

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) ሊቀመንበር የቤት ውስጥ የመታሰር ጉዳይን አስመልክቶ ለፌደራል ፓሊስ ኮሚሽን እና ለብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት መስሪያ ቤቶች ደብዳቤ ፅፏል።

የፖለቲካ ፓርቲዎችን አቤቱታ የሚያጣሩ ቡድኖች ወደ አቶ ዳውድ ኢብሳ ቤት የካቲት 21 ቀን 2014 ዓ/ም በመሄድ አቶ ዳውድ ያሉበትን ሁኔታ አጣርተዋል።

አጣሪዎቹ በሪፖርታቸው እንዳቀረቡት የቡድኑ አባላት የሊቀመንበሩ መኖሪያ ቤት ሲደርሱ አንኳክተው የከፈቱላቸው ሲቪል የለበሱ የፀጥታ ሰራተኞች መሆናቸውን ማንም ሰው መግባት እንደማይፈቀድለት ገልፀው ገብተው ለማየት መጀመሪያ ፍቃድ መጠየቅ ያለበት መሆኑን ከየት እንደመጡና ለምን እንደመጡ መጠየቃቸውን፣ በመጨረሻ እንዲጎበኟቸው መፈቀዱን ገልፀዋል።

የቡድኑ አባላት ከአቶ ዳውድ ኢብሳ ጋር ከመገናኘታቸው በፊት የያዙት ቦርሳ መፈተሹን እንዲሁም ስልካቸውን ይዘው መግባት እንደማይችሉ እንደተገለፀላቸው በመጨረሻም ይህን ፈፅመው ከአቶ ዳውድ ጋር እንደተገናኙ ለቦርዱ ሪፖርት አቅርበዋል።

የአጣሪ ቡድኑ አባላት ከአቶ ዳውድ ጋር ባደረጉት ውይይት የተረዱት ከመጋቢት 24 /2013 ዓ /ም ጀምሮ ከቤት እንዳይወጡ የታጠቁ ሰዎች ግቢያቸው ውስጥ ተመድበው የከለከሏቸው መሆኑን ነው።

ምርጫ ቦርድም አቶ ዳውድ ኢብሳ የቤት ውስጥ እስረኛ ሆነው የመንቀሳቀስ መብታቸው እንደተገደበ ተገንዝቧል።

በመሆኑም ቦርዱ እኚህ የፓርቲ አመራር በየትኛውም የህግ አግባብ ተቀባይነት በሌለው ሁኔታ የሚገኙበትን የቤት ውስጥ እስር በአፋጣኝ መቆም እንዳለበት አስገንዝቧል።

ተቋማቱ በአቶ ዳውድ ኢብሳ ግቢ የመደቡትን ጥበቃ እንዲያነሱና የሊቀመንበሩን የመንቀሳቀስ መብት አስከብረው በአስቸኳይ ለቦርዱ እንዲገለፁም አሳውቋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ሩስያ ፥ ስዊድንን እና ፊንላንድን አስጠነቀቀች። የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ስዊድን እና ፊንላንድ NATOን ለመቀላቀል ከሞከሩ " ጎጂ " የሆኑ ውጤቶች [ ኢኮኖሚያዊ እና ወታደራዊ ] እንደሚኖሩ አስጠንቅቋል። አሁን በዩክሬን እና ሩስያ መካከል ያለው ጦርነት ተባብሶ በቀጠለበት ሁኔታ ሩስያ ፊንላንድ እና ስዊድንን ማስፈራራቷ ሌላ ዓለም አቀፋዊ ስጋት ፈጥሯል። የኃያላን ሀገራቱ ግብግብ በተለይ…
#NATO

NATO በዩክሬን እየተካሄደ ስላለው ጦርነት ሁሉንም መረጃዎች የቅርብ አጋሮቼ ናቸው ላላቸው ስዊድን እና ፊንላንድ እያካፈለ መሆኑን ዋና ጸሃፊው ጄንስ ስቶልተንበርግ ዛሬ አስታውቀዋል።

ስቶልተንበርግ ዛሬ በብራስልስ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ “ለሩሲያ ወረራ ምላሽ ለመስጠት ከፊንላንድ እና ስዊድን ጋር ያለንን ትብብር እና የመረጃ ልውውጥ ለማጠናከር ወስነናል " ብለዋል።

አክለውም ፥ " ሁለቱም ሀገሮች አሁን ላይ ስለ ቀውሱ በሁሉም የNATO ምክክር እየተሳተፉ ነው። ” ሲሉ ተደምጠዋል።

ከቀናት በፊት ሩሲያ ፥ ስዊድን እና ፊንላንድ NATOን ለመቀላቀል #ከሞከሩ " ጎጂ " የሆኑ ውጤቶች [ ኢኮኖሚያዊ እና ወታደራዊ ] እንደሚኖሩ አጥብቃ ማስጠንቀቋ የሚዝነጋ አይደለም።

ሩስያ ሁለቱን ሀገራት አርፋችሁ ቁጭ በሉ ስትል ማስጠንቀቋ በዩክሬን ተባብሶ የቀጠለው ጦርነት ላይ ሌላ ከፍተኛ ዓለም አቀፋዊ ስጋት እና አደጋ ሊፈጥር እንደሚችል ሲነገር እንደነበር ይታወሳል።

አሁን ላይ ምንም እንኳን ሁለቱ ሀገራት የNATO አባል ባይሆኑም NATO ከሁለቱም ሀገራት ጋር ያለውን ገኙነት ይበልጥ ለማጠናከር ወስኗል።

@tikvahethiopia
#ማሳሰቢያ

በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በመጀመሪያ ዲግሪ መርሀ ግብር ለመማር የሚመዘገቡ ተማሪዎች የሚከተሉትን የቅበላ መስፈርቶችን ማሟላት እንደሚኖርባቸው የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ትምህርት እና ስልጠና ባለሥልጣን አስታውቋል።

እነዚህም፡-

1. የመሰናዶ ትምህርት ያጠናቀቁ ተማሪዎች ከሆኑ ትምህርት ሚኒስቴር ለትምህርት ዘመኑ ያስቀመጠውን የመቁረጫ ነጥብ ሊያሟሉ ይገባል፡፡

2. ከቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ተቋም የተመረቁ ባለሙያዎች ከሆኑ ከሠለጠኑበት የሙያ መስክ ጋር ተዛማጅነት ባለው የሥልጠና መስክ በአዲሱ የትምህርት ፖሊሲ በደረጃ 4 (ወይም በቀድሞ 10+3 ወይም 12+2) ያጠናቀቁ ሆነው በሙያው ደረጃ 4 የብቃት ማረጋገጫ ምዘና (COC level 4) ተፈትነው ያለፉበትን፤ እንዲሁም በሙያው ቢያንስ የሁለት ዓመት ሥራ ልምድ ያላቸው መሆኑን የሚያረጋግጡ ማስረጃዎች በምዝገባው እለት ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፡፡

3. ከውጭ ሀገር የተገኘ የትምህርት ማስረጃ ለዲግሪ መርሃ-ግብር መግቢያ የሚያገለግለው በባለስልጣኑ የአቻ ግምት ሲሰራለት ብቻ ይሆናል፡፡

4. በየተቋማቱ የሚዘጋጁትን የመግቢያ ፈተናዎች ማለፍ ይጠበቅባቸዋል፤ ከላይ የተጠቀሱትን መስፈርቶች በምዝገባው ዕለት ማቅረብ ያልቻለ ተመዝጋቢ ህጋዊ ተቀባይነት አይኖረውም።

ከላይ የተጠቀሱትን እና ሌሎች ህጋዊ መመሪያዎችን ጥሶ የተገኘ ተቋም በከፍተኛ ትምህርት ተቋም የስነ ስርዓት መመሪያ መሠረት በህግ ተጠያቂ እንደሚሆን የተገለፀ ሲሆን ከህግ ውጪ ገብተው የሚማሩ ተማሪዎችም ሊደርስባቸው የሚችለውን የጊዜ፣ የገንዘብና የስነ-ልቦና ኪሳራ አውቀው አስፈላጊውን ቅድመ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ባለስልጣኑ አሳስቧል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ASTU #AASTU ሁለቱ የኢትዮጵያ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲዎች የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ተፈትነው ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የሚያስገባ ነጥብ ያዝመዘገቡ ተማሪዎችን ለመቀበል በዛሬው ዕለት ጥሪ አቅርበዋል። ዩኒቨርሲቲዎቹ የ2014 ዓ.ም መግቢያ ፈተና የምዝገባ ጥሪ አውጥተዋል። የመመዝገቢያ መስፈርቱ የሲቪክስ ትምህርትን ሳይጨምር የስድስት ትምህርት ድምር ውጤት ከዚህ በታች እንደተገለፀው…
#የተሻሻለ

የኢትዮጵያ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲዎች የ2014 ዓ.ም መግቢያ ፈተና የምዝገባ ጥሪ መስፈርቶች ላይ ማሻሻያ ተደርጎበታል።

የመመዝገቢያ መስፈት የሲቪክስ ትምህርትን ሳይጨምር የስድስት ትምህርት ድምር ውጤት መሆኑ ተገልጿል።

• ለአዳጊ ክልሎች (አፋር፣ ሱማሌ፣ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ እና ጋምቤላ)

- ኢንጂነሪንግ ~ ለወንድ 375፣ ለሴት 370
- አፕላይድ ሳይንስ ~ ለወንድ 365፣ ለሴት 360

• ለሌሎች ክልሎች

- ኢንጂነሪንግ ~ ለወንድ 380 ፣ ለሴት 375
- አፕላይድ ሳይንስ ~ ለወንድ 370፣ ለሴት 365

የምዝገባ ጊዜው ከየካቲት 21 እስከ 30/2014 ዓ.ም ሲሆን ምዝገባው የካቲት 30 /2014 ዓ/ም ከለሊቱ 6 ሰዓት ይጠናቀቃል ተብሏል።

የምዝገባ መስፈርቱን የሚያሟሉ በኢንተርኔት www.aastu.edu.et እና www.astu.edu.et ላይ መመዝገብ ይችላሉ።

የመግቢያ ፈተናው መጋቢት 07/2014 ዓ.ም ይሰጣል። (ተጨማሪ መረጃ ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia