TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ከሃዋሳ~አዳሬ ሆስፒታል👆

"በሃዋሳ ከተማ ~~ በሀዋሳ አዳሬ ሆስፒታል "ፊቼ ጫምባላላን" በማስመልከት የደም ልገሳ መርሃ ግብር እየተካሄደ ይገኛል።"

ደም በመለገስ ህይወት እናድን!!

Via Dr. Hanibal Abera /TIKVAH-ETH/
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ለ2ኛ ጊዜ #የናይጄሪያ ፕሬዝዳንት ሆነው የተመረጡት ሙሃመዱ ቡሃሪ እና ምክትላቸው ፕሮፌሰር ዬሚ ኦሲንባጆም በዛሬው እለት በዋና ከተማዋ በአቡጃ ቃለ መሃላ ፈፅመዋል፡፡

ሙሃመዱ ቡሃሪ የፕሬዝዳንትነቱ ስልጣን የመጨረሻቸው እንደሆነ ነው የተገለፀው፡፡

ፕሬዝዳንቱ ባለፈው ይካቲት በተደረገው ዳግም ምርጫ ከ15 ሚልዮን በላይ መራጮችን ድምፅ አግኝተው ነበር ዳግም የተመረጡት፡፡

ድምፅ ለመስጠት ከተመዘገቡት 84 ሚሊዮን መራጮች መካከል 35 በመቶ የሚሆኑት ብቻ ነበር ድምፅ የሰጡት፡፡

በበዓለ ሲመቱ የ29ኙም የናይጄሪያ ግዛቶች ዋና ገዢዎችን፣ ጨምሮ የሐገሪቱ ከፍተኛ ባለመስጣናት ተሳትፈዋል፡፡

ምንጭ፡- አፍሪካን ኒዉስ/etv/
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update በአቶ #ዳውድ_ኢብሳ የሚመራው ኦነግ ከኦዴፓና ከኦሮሚያ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ጋር በጋራ ለመስራት ተስማማ።በሃገር ውስጥ ሲንቀሳቀስ የነበረውን የኦነግ ታጣቂ ወደ ካምፕ ለማስገባት የተሰራው ስራ ላይ የማጠቃለያ ሪፖርት ዛሬ ቀርቧል። ሪፖርቱ በመንግስትና በኦነግ የዕርቀ ሰላም ኮሚቴና የሃገር ሽማግሌዎች አማካኝነት፥ የኦሮሚያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ፣ የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ማዕከላዊ ፅህፈት ቤት ሃላፊ አቶ አዲሱ አረጋ እና የኦነግ ሊቀ መንበር አቶ ዳውድ ኢብሳ በተገኙበት ነው የቀረበው።

ከሪፖርቱ በኋላ የኦሮሚያ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት፣ የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ እና የኦነግ አመራሮች፥ የክልሉን ህዝብ ተጠቃሚነትና አንድነት ለማረጋገጥ በጋራ እንደሚሰሩ አስታውቀዋል። ኦነግ የክልሉ መንግስት የህግ የበላይነትን ለማረጋገጥ የሚሰራቸውን ስራዎች #እንደሚደግፍም ሊቀመንበሩ አቶ ዳውድ ኢብሳ ተናግረዋል። አያይዘውም ከዚህ በኋላ ታጥቆ የሚንቀሳቀስ ሰራዊት እንደማይኖርም ገልፀዋል።

Via #FBC
ፎቶ፦ #ጃዋር_መሃመድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update በሃገር ውስጥ ሲንቀሳቀስ የነበረውን #የኦነግ ታጣቂ ወደ ካምፕ ለማስገባት የተሰራው ስራ ላይ የማጠቃለያ ሪፖርት ቀረበ። ሪፖርቱ በመንግስትና በኦነግ የዕርቀ ሰላም ኮሚቴና የሃገር ሽማግሌዎች አማካኝነት፥ የኦሮሚያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ፣ የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ማዕከላዊ ፅህፈት ቤት ሃላፊ አቶ አዲሱ አረጋ እና የኦነግ ሊቀ መንበር አቶ ዳውድ ኢብሳ በተገኙበት ነው የቀረበው።

ከሪፖርቱ በኋላ የኦሮሚያ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት፣ የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ እና የኦነግ አመራሮች፥ የክልሉን ህዝብ ተጠቃሚነትና አንድነት ለማረጋገጥ በጋራ እንደሚሰሩ አስታውቀዋል። ኦነግ የክልሉ መንግስት የህግ የበላይነትን ለማረጋገጥ የሚሰራቸውን ስራዎች እንደሚደግፍም ሊቀ መንበሩ አቶ ዳውድ ኢብሳ ተናግረዋል።

Via #BBC
ፎቶ፦ ጃዋር መሃመድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የኢትዮጵያ አየር መንገድ የብሉምበርግ ዘገባን አጣጣለ። ብሉምበርግ ዛሬ ባስነበበው ዘገባ በኢቲ 302 ከመከስከሱ በፊት የአየር መንገዱ ፓይለት ለአለቆቹ አደጋ ሊደርስ እንደሚችል አስጠንቅቆ ነበር ብሏል።

የብሉምበርግ ዘገባ እንደሚለው ከሆነ ብረንድ ካይ ቮን ሆሰሊን የተባለው የኢትዮጵያ አየር መንገድ አብራሪ ከአደጋው በፊት ማለትም ታህሳስ 4 2011 ዓ.ም. ለከፍተኛ የአየር መንገዱ ባለስልጣናት በላከው ኢሜይል የኢንዶኔዢያ አየር መንገድ አይነት አደጋ እንዳይከሰት ቦይንግ 737 ማክስ አውሮፕላኖችን በተመለከተ ለኢትዮጵያ አየር መንገድ አብራሪዎች ተጨማሪ ስልጠና እና የግንኙነት ዘዴዎችን በተመለከተ ስልጠና መሰጠት አለበት ብሏል።

የኢሜይል መልዕክቱን ተመልክቸዋለሁ የሚለው ብሉምበርግ፤ ኢሜይሉን ጽፏል የተባለውን ብረንድ ካይ ቮን ሆሰሊን አግኝቶ ማነጋገር አለመቻሉን እና የኢሜይል መልዕክቱንም ያገኘው ስሙ እንዲጠቀስ ከማይሻ ግለሰብ እንደሆነ በዘገባው አስፈሯል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በበኩሉ የቡሉምበርግ ዘገባ የተሳሳተ ነው ሲል መግለጫ አውጥቷል። በመግለጫውም የብሉምበርግ ዘገባ ሙሉ በሙሉ መሰረተ ቢስ እና እውነታ የሌለው ነው ብሎታል።

‘‘በዘገባው ላይ የዜናው ምንጭ ሆኖ የተጠቀሰው አብራሪ በስነ-ምግባር ጉድለት እና የድርጅቱን አሠራር መከተል ባለመቻሉ ከአየር መንገዱ ጋር የነበረው የሥራ ስምምነት በአጭሩ የተቋረጠበት ግለሰብ ነው’’ ብሏል አየር መንገዱ።

መግለጫው አክሎም አብራሪው የኢትዮጵያ አየር መንገድ በዓለም አቀፍ ደረጃ ያካበተውን ዝና ለማጠልሸት እየሰራ ስለሆነ የኢትዮጵያ አየር መንገዱ ሕጋዊ እርምጃ ይወስዳል ሲል ያትታል።

ከዚህ ቀድም ይፋ ተደርጎ የነበረው የኢቲ 302 የመጀመሪያ ደረጃ ግኝቶች አብራሪዎቹ ይህንን በረራ ለማድረግ የሚያችላቸው ብቃትና የምርመራ ፍቃድ እንደነበራቸው እንዲሁም አብራሪዎቹ አውሮፕላኑን ለመቆጣጠር ያስችላል የተባለውን ቅድም ተከተል ቢፈጽሙም እንዳልተቻላቸው ይፋ ማደረጉ ይታወሳል።

Via #BBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የሃምሊን ፊስቱላ ማዕከል መሥራች ዶ/ር ካትሪን ሃምሊን ሐውልት ጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ አሕመድ በተገኙበት ተመረቀ። ሐውልታቸው የቆመው በአዲስ አበባ ጦር ኃይሎች በሚገኘው የሃምሊን ፊስቱላ ሆስፒታል ውስጥ ሲሆን ጠቅላይ ሚንስትሩም ሆስፒታሉን ጎብኝተዋል።

"ዶ/ር ሃሚሊን ለምን እንደተፈጠሩ ያወቁ እድለኛ እናት ናቸው” ጠ/ሚ ዶ/ር #አብይ_አህመድ

@tsegabwolde @tikvahethiopia
"GALANNI KAN RABBI GUDDAATI. Asiin nu gahe. Waliigaltee taba haphee itti godhee nuuf haa maxxansu. Odeeffannoo guutuuf gabaasa miidiyaalee daaw’adhaa."

Via #Jawar_Mohammed
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#UpdateSport የአውሮፓ ሊግ የፍጻሜ ጨዋታ በአዘርባጃኗ ዋና ከተማ ባኩ መካሄዱ ብዙ ቅሬታዎችን አስነስቷል።

የፊታችን ቅዳሜ የሚደረገው የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ የፍጻሜ ጨዋታ ላይ ለመታደም ብዙ እንግሊዛውያን ወደ ስፔኗ መዲና ማድሪድ እንደሚጎርፉ ይጠበቃል።

ነገር ግን ዛሬ የሚካሄደውን የአውሮፓ ሊግ የፍጻሜ ጨዋታ ለማየት ወደ አዘርባጃን መዲና ባኩ መምጣት የሚችሉት የአርሰናልና የቼልሲ ደጋፊዎች ቁጥር ከ6000 እንደማይበልጥ ተገልጿል።

ከዚህ በተጨማሪ የአርሰናሉ ሄነሪክ ሚኪታሪያን #በአርሜኒያዊ ዜግነቱ ምክንያት ደህንት አይሰማኝም በማለት ወደ አዘርባጃን እንደማይሄድ አስታውቋል። አርሜኒያ እና አዘርባጃን 'ናጎርኖ ካራባክ' የተባለው #ክልል የይገባኛል ፍጥጫ ውስጥ ያሉ ሲሆኑ የሚኪታሪያንም #የስጋት ምንጭ ይሄው ነው።

ብዙዎችም የፍጻሜ ጨዋታውን ለምን በአዘርባጃን ማካሄድ አስፈለገ? በማለት ቅሬታቸውን እየገለጹ ነው። የአውሮፓ እግር ኳስ ማህበር ግን ሃገሪቱ ለምስራቅ አውሮፓ ሩቅ በመሆኗ ምክንያት ውድድሩን ከማዘጋጀት ልትታገድ አይገባም ብሏል።

ባላት የነዳጅ ሃብት ምክንያት እጅግ የበለጸገችው አዘርባጃን ብዙ ሚሊዮን ዶላሮችን ፈሰስ በማድረግ በዓለማቀፍ ስፖርት ቤተሰቦች ዘንድ ያላትን ተቀባይነት ከፍ ለማድረግ እየሰራች ነው።

Via #ቢቢሲ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አሳዛኝ ዜና‼️

በቶክዮ አንዲት ተማሪና አንድ ጎልማሳ መገደላቸው ተገለፀ። በሁለት እጆቹ #ቢላ የያዘ ሰው "ካዋሳኪ" በተባለች ከተማ ተማሪ ሴቶች፣ አውቶብስ ሲጠበቁ በነበሩበት ቦታ ላይ ደርሶ በቢላ ማጥቃት እንደጀመረ ተዘግቧል።

በሃምሳ ዓመታት ዕድሜ ክልል ውስጥ የነበረው አጥቂ፣ ራሱን በቢላ ወግቶ እንደገደለ የጃፓን ብሄራዊ ማሰራጫ ዘግቧል።

የተገደሉት ሰዎች የ12 ዓመት ዕድሜ ተማሪ ሴትና የ39 ዓመት ዕድሜ ወንድ ናቸው ተብሏል። ሦስት ሰዎች ላይ ከባድ ጉዳት ደርሶባቸዋል።

Via #VOA24
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የገዛ ባሏን በመርዝ የገደለችው ተከሳሽ በ19 ዓመት ጽኑ እስራት መቀጣቷን የምሥራቅ ወለጋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት አስታወቀ፡፡

የዞኑ ከፍተኛ ፍርድ ቤት የወንጀል ችሎት ሰብሳቢ ዳኛ አቶ ዋቁማ ጡሪ እንዳስታወቁት በነቀምቴ ከተማ አስተዳደር 03 ቀበሌ ውስጥ በምትኖረው ተከሳሽ ወይዘሮ እልፍነሽ በቀለ ጅራታ ላይውሳኔው የተላለፈው ባሏን አቶ አዳነ አሰፋውን በመርዝ መግደሏ በመረጋገጡ ነው።

ሟች ከኦሮሚያ ብድርና ቁጠባ አክሲዮን ማህበር ከተበደሩት 86ሺህ ብር ውስጥ 10ሺህ ብር እንዲሰጣት ጠይቃ ፍቃደኛ ባለመሆኑ ቂም ይዛ መርዝና አይብ በማደባለቅ መጋቢት 01/2011ዓ.ም ከምሽቱ በግምት አራት ሰዓት አካባቢ እንዲመገብ አድርጋለች።

ወደ መኝታ ክፍል እንደገባም በሩን በውጭ በኩል ዘግታ መሞቱን ካረጋገጠች በኋላ ራሱን በራሱ የገደለ ለማስመሰል ’’ፀፀት’’ ተብሎ የተፃፈና ሁለት ገጽ ያለው ወረቀት በደረቱ ላይ አስቀምጣ መኖሪያ ቤቱን በመዝጋት ንብረት ስታሸሽ መያዟን አመልክተዋል።

የተከሳሿ ድርጊት በዞኑ ዓቃቤ ሕግየሕግ ምሥክሮች በመረጋገጡ፣ ራሷም የፈጸመችውን ድርጊት ማመኗንና የመከላከያ ማስረጃም የለኝም ማለቷን አቶ ዋቁማ አስረድተዋል፡፡

በመሆኑም የዞኑ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በግንቦት 21/2011 ዓ.ም በዋለው ችሎት ተከሳሿ ሆን ብላ የሰውን ሕይወት ለማጥፋት ተዘጋጅታ የፈጸመችው ድርጊት በመሆኑ በ19 ዓመት ጽኑ እስራት እንድትቀጣ መወሰኑን ገልጸዋል፡፡

Via #ENA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update 2 ሚሊዮን 255 ሺ 880 ብር የሚያወጡ ልዩ ልዩ የኮንትሮባንድ እቃዎቹ በሞያሌ ጉምሩክ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ስር በሚገኙ በቡሌ ሆራና ያቤሎ መቆጣጠሪያ ጣቢያ ግንቦት 19/2011 ዓ.ም ነው በቁጥጥር ስር የዋሉት፡፡ የኮንትሮባንድ እቃዎቹ በቁጥጥር ስር የዋሉት የጉምሩክ ሰራተኞች ባደረጉት ፍተሻ እንደሆነ ቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ገልጿል፡፡

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ተማሪዎች ግቢውን ለቀው ወጥተዋል...

በደብረ ማርቆስ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች መካከል ባለፈዉ ሳምንት ማብቂያ በተፈጠረ ግጭት ምክንያት ቁጥራቸዉ በዉል ያልተገለፀ ተማሪዎች የዩኒቨርስቲዉን ግቢ ለቀዉ መዉጣታቸዉ ተዘገበ።

Via #DW

https://p.dw.com/p/3JT7C?maca=amh-RED-Telegram-dwcom
ከሃዋሳ ...

"በፎቶው የምትለመከቷት የሲዳማ እናት ነገ እና ከነገ ወዲያ ለሚከበረዉ ፊቼ ጨምበላላ የሚቀርብ ግሩም የሆነዉን የሲዳማ ባህላዊ ምግብ "ቡሪሳሜ"ን ለማዘጋጀት የምትኳትን እናት ነች። ግሩሙን "ቡሪሳሜ" በ "ጌእንቶ"(እርጎ ወተት) ለመመገብ በበዓሉ ቀን ሀዋሳ ከች ማለት!! ኑና አብረን በዓለም የጋራ ቅርሳችን የሆነዉን ፊቼ ጨምባላላን በዓል አብረን በዉቢቱ ሀዋሳ-አዳሬ እናክብር!! Peoples are gathered in to #Hawassa-Adare from tomorrow on to celebrate The new year of Sidama people Fichee Chambalallal...Lets celebrate together!!"

Via #Job
@tsegabwolde @tikvahethiopia