TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
የገቢዎች ሚኒስቴር🔝

ከላይ የምትመለከቱት #በታክስ_ኦፕሬሽን #ደረሰኝ_ባለመቁረጥ የተያዙ የ65 ድርጅቶች ዝርዝር ነው።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update በኢ.ፌ.ዲ.ሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዶ/ር #ወርቅነህ_ገበየሁ ሰብሳቢነት ዛሬ የካቲት 20 ቀን 2011 ዓ.ም በጅቡቲ የተካሄደው 46ኛው የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት (ኢጋድ) የሚኒስትሮች ካውንስል ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት የተለያዩ ውሳኔዎችን በማሳለፍ ተጠናቋል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ቤንሻንጉል ጉምዝ‼️

በአሶሳ ወረዳ ከ190 በላይ የሚሆኑ የሚሊሺያ አባላት ከክልሉ መንግስት እውቅና ውጭ #ወታደራዊ ስልጠና መውሰዳቸው ተገለፀ። ይህን ባደረጉ አመራሮች ላይም ህጋዊ #እርምጃ ተወስዶባቸዋል።

በክልሉ የሰላም ግንባታና የፀጥታ ቢሮ የሚሊሺያ ዘርፍ ሃላፊ አቶ #ደርጉ_ዚያድ ለኢቢሲ እንደተናገሩት በክልሉ ደረጃ የሚሊሺያ ሰራዊትን በአዲስ መልክ ለማደራጀት እየተሰራ ነው ብለዋል።

ከሰሞኑ የሚሊሺያ ሰራዊት አባላት ግምገማ የተካሄደ ሲሆን ለውጡን ማስቀጠል የሚችል የሚሊሺያ ሰራዊት መዋቅር ለመዘርጋት በሚያስችል መልኩ ግምገማ ተካሂዷል። በዚህም ከአሶሳ ወረዳ ብቻ 140 የሚሊሺያ አባላት በክብር ተሰናብተዋል። እንዲሁም ሰኔ 17 በአሶሳ ከተማ ተከስቶ በነበረው ግጭት የተጠረጠሩ 9 የሚሊሺያ አባላት በህግ #ቁጥጥር ስር ውለዋል።

በአሶሳ ወረዳ 190 የሚሆኑ የሚሊሺያ ሰራዊት ከክልሉ መንግስት እውቅና ውጭ ወታደራዊ ስልጠና ወስደዋል ያሉት አቶ ደርጉ ይህን ባደረጉ አካላት ላይ ህጋዊ እርምጃ ተወስዶባቸው ብለዋል። የክልሉን የሚሊሺያ ሰራዊት በአዲስ መልክ ለማደራጀት እየተሰራ መሆኑን አቶ ደርጉ ለኢቢሲ ተናግረዋል።

Via ebc
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ገበታ_ለሸገር

እራቱን ለመታደም የምትፈልጉ...

ለቢዝነስ ባለቤቶች፣ የኩባንያ ሥራ አስፈጻሚዎች፣ ዓለም አቀፍ ድርጅት ኃላፊዎችና የዲፕሎማቲክ ማኅበረሰብ አባላት፦

ሸገርን የማስዋብ ፕሮጀክት ለመደገፍና ከጠቅላይ ሚኒስትር #ዐቢይ_አሕመድ ጋር ገበታ ለመቅረብ sheger@pmo.gov.et ላይ ፍላጎትዎን እንዲገልፁ ጥሪ ቀርቧል።

የእራቱ ዋጋ በሰው -- ብር 5ሚሊዮን!

ሙሉ ስምዎን፣ ድርጅትዎን፣ የተንቀሳቃሽ ስልክ ቁጥርዎን ሲልኩ በሸገር ገበታ ለመታደም የመመዝገቢያ ቅጽ ይላክሎታል።

#PMOEthiopia
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የአባገዳን ጥሪ በማክበር በሰላማዊ መንገድ ለመታገል የወሰኑ የኦነግ ታጣቂዎች በዛሬው ዕለት ወደ #ጦላይ_ማሰልጠኛ ካምፕ ገብተዋል፡፡

via etv
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ #ደመቀ_መኮንን 5ተኛው የኢትዮ~ሱዳን ከፍተኛ የጋራ ኢኮኖሚ ትብብር ጉባዔ ላይ ለመሳተፍ ሱዳን~ካርቱም ገብተዋል። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ ካርቱም ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ጣቢያ እንደደረሱ፤ የሱዳን ምክትል ፕሬዚዳንት #ኦስማን_መሃመድ_ዩሱፍ_ኪቢር በወታደራዊ ማርሽ የታጀበ ደማቅ አቀባበል አድርገውላቸዋል።

Via Office of Deputy Prime Minister of Ethiopia
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የወላይታ ሶዶ ውሎ‼️

በደቡብ ክልል በወላይታ ሶዶ ከተማ ዙሪያ ህገወጥ የተባሉ ቤቶች #መፍረሳቸውን ተከትሎ በከተማይቱ ዛሬ ግርግር እንደነበር ነዋሪዎች ተናገሩ። በከተማይቱ #የተኩስ ድምጽ ይሰማ እንደነበርም የዓይን እማኞቹ ገልጸዋል።

አቶ ዳንኤል ዓለሙ የተባሉ የከተማይቱ ነዋሪ ለጀርመን ራድዮ እንደተናገሩት በከተማይቱ #ግርግር የተቀሰቀሰው ዛሬ እኩለ ቀን አካባቢ ነበር። የግርግሩ መነሻም በተለምዶ “የጨረቃ ቤቶች” ተብለው የሚጠሩ በከተማይቱ ዙሪያ ከተገነቡ መኖሪያ ቤቶች መፍረስ ጋር የተያያዘ እንደሆነም ገልጸዋል። “በጣም ግርግር ነበር። የተወሰነ ጥይት ተኩሰዋል። ሰው ሩጫ ላይ ነበር” ሲሉ የነበረውን ሁኔታ ገልጸዋል።

ስማቸው እንዳይገለጽ የጠየቁ ሌላ የከተማይቱ ነዋሪም ከቀኑ ስድስት በኋላ ጥይት ይሰማ እንደነበር አረጋግጠዋል። የቤቶችን መፍረስ በመቃወም መንገድ ዘግተው የነበሩ ሰዎችን ለመበተን ፖሊስ አስለቃሽ ጭስ መተኮሱንም የዓይን እማኙ ገልጸዋል። ግርግሩን የፈሩ ሱቆች እና ምግብ ቤቶች ተዘግተው መዋላቸውን የሚናገሩት እኚሁ ነዋሪ ወደ 10 ሰዓት ገደማ ግን ከተማይቱ “ወደ ሰላማዊ ሁኔታ ተመልሳለች” ብለዋል።

በወላይታ ሶዶ ህገወጥ ናቸው የተባሉ ቤቶች እየፈረሱ የሚገኙት ቀድሞ የገጠር ቀበሌዎች የነበሩ ነገር ግን ከአንድ ዓመት ወዲህ በከተማይቱ ክልል ስር በተካተቱ ሶስት አካባቢዎች እንደሆነ ነዋሪዎች ለDW አስረድተዋል። ላሬና፣ ኦፎሳሬ እና ቆንቶ በተባሉት በእነዚህ ቦታዎች የእየፈረሱ ያሉት ቤቶች በመቶዎች የሚቆጠሩ እንደሆኑ ነዋሪዎቹ ገልጸዋል።

የወላይታ ሶዶ ከተማ ባህል፣ ቱሪዝም እና የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት የኮሚዩኒኬሽን የስራ ሂደት አስተባባሪ አቶ መንግስቱ ቶራ ዛሬ በከተማይቱ የተፈጠረው ግርግር “የህገ ወጥ ግንባታን ለመከላከል እየተደረገ ካለው እንቅስቃሴ ጋር የተያያዘ አይደለም” ሲሉ አስተባብለዋል። “ሰባት ሰዓት አካባቢ ጎማ በመቃጠሉ ሰዉ አመጽ ሊቀሰቀስ ነው በሚል ሰግቶ፣ ፈርቶ ነበር። ግን ምንም ነገር የለም። ተረጋግቷል” ሲሉ ለጀርመን ራድዮ ተናግረዋል።

የከተማይቱ የባህል፣ ቱሪዝም እና የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት ዛሬ በፌስ ቡክ ገጹ ባወጣው መግለጫ ካለፈው ከትላንት ጀምሮ የሶዶ ከተማ አስተዳደር እና በዙሪያ ያለው ወረዳ ህገወጥ ግንባታ የመከላከል እና የህግ የበላይነትን የማስከበር ስራ እየሰሩ እንደሚገኙ አስታውቋል። በህገወጥ ግንባታ ተሳታፊ የሆኑ ግለሰቦች “ስራውን ለማስተጓጎልና የከተማውን ጸጥታ ለማወክ” መሞከራቸውንም ጠቁሟል። “መንገድ በመዝጋት፣ ደን የማቃጠል ሙከራ በማድረግ እና ሌሎች ችግሮችን ለመፍጠር ሲንቀሳቀሱ ተደርሶባቸዋል” ያላቸው ግለሰቦችም “#በቁጥጥር ስር ውለዋል” ብሏል።

ምንጭ፦ የጀርመን ራድዮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia